ዮሐንስ ሞላ's Blog, page 10
September 26, 2017
ኢትዮጲያ: በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ግጭት! — Ethiopian Think Tank Group
አሁን ባለው የኢትዮጲያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ግራ-መጋባት ይታየኛል። ግራ መጋባቱ በዋናነት “ሀገሪቱ ወደየት እያመራች ነው?” በሚለው ጥያቄ ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ግራ መጋባት ታዲያ በአንዱ ወይም በሌላኛው ወገን ላይ ሳይሆን በሁሉም ወገኖች ላይ የሚስተዋል ነው። የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እና ደጋፊዎች፣ በብሔርተኝነት እና በአንድነት ጎራ በተሰለፉት ተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችና ደጋፊዎች ላይ በግልፅ ይስተዋላል። […]
via ኢትዮጲያ: በግራ መጋባት ወደ እርስ-በእርስ ግጭት! — Ethiopian Think Tank Group


June 7, 2017
ሱስቆት…
ሰሞኑን አገር ቤት ኢንተርኔት ከመቋረጡ ጋር ተያይዞ፥ ወዳጆች የፌስቡክ እና የሌሎች ማኅበራዊ ድረ ገጾች “ናፍቆት” እንዴት እንዴት እንዳደረጋቸው እያየን ነው። እኔም “መቼም የሸገር ጓዶቼ በሰፊው ብትን ያላሉበት ፌስቡክስ ቢቀር ይሻላል” ብዬ፥ ከፌስቡክ ለመራቅ ያደረግኩት ሙከራ ባጭሩ ሲከሽፍብኝና፣ ጣቴን እየበላኝ በባዶ ሜዳም… “ሄድኩ” ስል ስመለስ ከራሴ ጋር እየተሳሳቅኹኝም
“ኧረ ይኼ ነገር የከፋ ሳይሆን አልቀረም።” ብዬ “ከፌስቡክ ሱስ መላቀቂያ መንገዶች”ን በመፈለግ፣ በዚያውም ስለፌስቡክ እና ስለሱሱ ማንበብ ቀጠልኩ። (ሱስ የመሆኑ ብዛት፥ ሰው ሁሉ መጠቀም ቢያቆም እንኳን ብቻችንን መጥተን እንድናውደለድል የሚገፋፋን ስሜት አለ።) የሚገርመው ነገር ግን፥ መላቀቂያ መንገዶቹን እያነበብኩ ራሱ፣ በየመሀሉ ስንት ጊዜ ፌስቡኬን ቼክ እንዳደረግኩ እኔና እግዜሩ እናውቃለን። ሃሃሃ…
የተጠቆሙትን መንገዶች ሁሉ ሳነብ፥ በልጅነት “እስክሪብቶዬ የዛሬን ጻፊልኝ፣ ለነገ አስገዛለሁ” ብለን ቁልቁል ዘቅዝቀን እንደምናራግፋት፣ “ቆይ አሁን፣ ቆይ በኋላ፣ ቆይ ነገ” ስል፥ ባህሩ እሹሩሩ እያለኝ እንደሆነ በደንብ ገባኝ። “ወደ ሲዖል የሚወስዱ መንገዶች በማስተባበያ የተጠረጉ ናቸው።” (the road to hell is paved with excuses) እንዲል ፈረንጅ፥ ሳልቦዝን፥ ለማስተባበያዎቼ ሳይቀር ማስተባበያ ስፈልግ ቆየሁ።
በንባቤ መሀል “ድረ ገጾቹን ብሎክ ማድረግ” የሚል ጥቆማ ሳገኝ፥ “wow, this must be working” ብዬ blocksiteን ተጠቅሜ ብሎክ አደረግኩት። ችግሩ እየረሳሁት ብቅ ስል፥ አውቶ ፖፓፑ ሲያላግጥኝና ስስቅ ዋልኩ። ስቄም አላባራሁ። ከዚያም ቆይ የፌስቡክን ሱስ ለማስታመም እና ቀስ በቀስ ለመተው ብዬ፣ ተያያዥ ነገሮችን እያየሁ ለመቆየት ወሰንኩና፥ ‘how to unblock a site blocked by a blocksite’ ብዬ ፈለግኩና ማብሪያና ማጥፊያዋን (the switch) አገኘኋትና፥ ይኸው ቀጥታ ከመጠቀም በማብሪያና ማጥፊያ ወደመጠቀም ተዘዋውሬያለሁ።
“ሲጋራም ቢሆን ባንዴ ማቆም ጥሩ አይደለም። ከፓኬት ወደ 10፣ ከ10 ወደ 5 ነው” የሚሉትን አስታውሼ፥ ብሎክሳይቷን በፈረቃ አብቃቅቼ ለመጠቀም ወሰንኩና “ቆይ የዛሬን” ብዬ off አደረግኩት።

May 24, 2017
ፈተናዎች…
በወጨፎ የቆሸሸ ሱሪዬን ማራገፍ፣ በዝናብ የራሰ ፀጉሬን መጠራረግ እንደጀመርኩ አንዲት ህጻን እያለቀሰች ገባች። ሹራቡ የተተለተለ ዩኒፎርም ለብሳለች። በዝናብ የረጠቡ ደብተሮች በቀኝ እጇ ከደረቷ ጋር አጣብቃ ይዛ፣ ከእንባዋ ጋር ተቀላቅሎ ሊወርድ የሚለውን ንፍጧን ሳብ እያደረገች ታለቅሳለች። ከተማው ውስጥ ካሉ ቤቶች የነጻ ትምህርት ፈቃድ አግኝተን፣ ቁርስ (አምባሻ በሻይ) እዚያው ግቢ ውስጥ ተመግበው፣ ለምሳ ሽሮ ተቋጥሮላቸው ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ከምናግዛቸው 45 የተማሪዎች መሀል አንዷ ነበረች።
[…ተማሪዎቹ ጎዳና ላይ ያለፈ ያገደመውን ለምነው (ሲችሉም አምታተው) የሚኖሩ ወላጅ አልባዎች፣ ወይም ከወላጆቻቸው ጋር ተጋግዘው በልመና የሚተዳደሩ ናቸው። በወቅቱ የኮሚቴው አቅም ቁርስና ምሳ ማብላት ብቻ ስለነበር፥ ከትምህርት ቤት ሲመለሱ አማራጭ በማጣት ወደልመናው ያቀናሉ። ከዚህም ባሻገር፥ ወላጆቻቸው ት/ቤት ሲሄዱባቸው የገቢ እጥረት ስለሚያጋጥማቸው፣ ልጆቹ ትምህርት እንዲያቋርጡ እንቅፋት ይሆኑባቸዋል።
የእኛ ዋና ሥራ፥ የማይጠቀሟቸውን አልባሳት እና ወርሃዊ መዋጮ የሚያደርጉ አባላትን ማስተባበር፣ ለዕለት ዕለት ምግብ ማብሰያ የሚወጣውን ወጪ መጠየቅ፣ እንደ ዩኒፎርም እና ደብተር የመሳሰሉ ዓመታዊ ቁሶችን ጊዜያቸው ሲደርስ ማሟላት፣ እና ህጻናቱ ወገንተኝነት እንዲሰማቸው፣ በትምህርትም እንዳይዘናጉ ‘አለሁ’ የማለት ያህል ነበር። ለምግብ ሥራው የተቀጠረ ሰራተኛ ነበር። ከበጎ አድራጊ በተገኘ የቆርቆሮ እና የሰራተኛ ክፍያ ድጋፍም ኩሽና እና ለመመገቢያ መጠለያ እንዲሆን እንደነገሩ ተመቷል። ሥራው መንፈስን ቢያጽናናም፣ በውስጡ መፈጠርን የሚያስመኙ ብዙ ፈተናዎች ነበሩት…]
በትምህርቷም ምስጉን ሆና፥ ለሽልማት የወላጆች ቀን ጥሪ ሁላ መጥቶልን ያውቃል።
“ምን ሆነሽ ነው?” አልኳት፥ ‘ይህኔ አንዱ ጥጋበኛ ሰካራም መቷት ይሆናል’ ብዬ ግምቴን አስቀድሜ።
የሹራቧን እጅጌ ሰብስባ በመዳፏ ይዛ፣ በአይበሉባዋ ዐይኗን እየጠረገች “ደብተሬን ዝናብ አጠበው” ብላኝ እሪታዋን እንዳዲስ አቀለጠችው።
“አይዞሽ በቃ፣ ሌላ ደብተር እሰጥሽና ትገለብጪያለሽ” አልኳት።
“ፈተና ደርሷል። ገልብጬ አልደርስም።” ብላ እዬዬዋን ቀጠለች። ምን ይደረጋል?
በሌላ ጊዜ እንዲሁ አንድ ልጅ እያለቀሰ መጣ። እናት የሞተችበት ያህል ነው የሚያለቅሰው። “ምን ሆነህ ነው?” ሲባል፥
“አባቴ ዩኒፎርሜን ሸጦ ጠጅ ጠጣበት” አለን።
እንዲህ ያሉ ብዙ ዓይነት ፈተናዎች ነበሩ።
ዩኒፎርሙን ደብቃ፥ “ጠፋብኝ ብለህ ተቀበል” ብላ የላከችም እናት ገጥማን ታውቃለች። ተስፋ ማየታቸው ሲታይ ግን ለራስም ትልቅ ተስፋ ይሰጥ ነበር።
[image error]ይሄ ትዝ ያለኝ፥ ሰሞኑን በVOA Amharic በኩል ከወደ ሀረርጌ የሰማነውን የመምህር ተስፋ አለባቸውን 40 ልጆችን ከጎዳና አንስቶ፣ ከሆቴል በተራረፈ ምግብ ወደ ትምህርት ቤት የመላኩ ቢያስደንቀኝ ነው። ልጆቹ የተረጂነት ስሜት እንዲያድርባቸው የማይፈልገው ተስፋ፥ የጠየቀው ነገር፣ ለልጆቹ ቋሚ ገቢ ማግኛ እንዲሆን የእንጀራ መጋገሪያ ምጣዶች እና የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች እንዲገዙለት ነው። ከ4 ቀናት በፊትም፥ ከሌሎች ወዳጆች ጋር ሆነን የጠየቀውን ገንዘብ እና ተጨማሪ የ6 ወር ወጪ ይሆናል ያልነውን ለማሰባሰብ የgofundme ገጽ (https://www.gofundme.com/40-dreams-40-hopes-one-donation) ተከፍቶ ይህ ጽሁፍ እስከተለጠፈበት ጊዜ ድረስ፣ በ65 ሰዎች መዋጮ $3,590 ማግኘት ተችሏል። (ሊንኩን ተከትለው ሙሉ ታሪኩን ያንብቡ።)
ዕቅዱን ለማሳካት የቀረው እንዲሟላ፣ የምትችሉ ከ$5 ጀምሮ በማዋጣት ልጆቹን “አይዟችሁ፣ በርቱ” እንበላቸው። ያልቻላችሁ፣ በማትችሉበት ሁኔታ ያላችሁ ደግሞ፥ መልእክቱን SHARE ብታደርጉት፣ ሌላ አቅምና ሁኔታ የሚፈቅድለት ሰው አይቶት እንዲያግዝ ምክንያት ትሆኑታላችሁና፥ አደራ!


May 13, 2017
Adey/አደይ

May 12, 2017
My mom!
everything she has,
and everything she hasn’t;
everything she never thought
that she would look for:
as her eternal need is
sandwiched between my nerves.
I’m everything to her,
she buys everything in me,
and she has a faith in me
and all the hope with in me.
If not my being
is there, in anything,
it all means nothing
for her, as I am big,
bigger than the world
and than anything it could offer.
But, I am everything,
even when there is nothing.
It is my usual perplexity that
her eyes give me wings
that I couldn’t touch;
but I see, whenever I see her,
my soul overwhelmingly swing.
She has been the light
whenever I get in a dark
that I survived the hardness
of the darkness;
and a life saver shade,
when the sun is over my heart.
I always have been defiant.
But, growing up,
even after prepubescence
I wouldn’t do, what she’d decry
or she wouldn’t like to be done,
and would make her heart cry;
[something, if done
that she would die to undone.]
Her soul has been
a red line that I won’t cross,
if not discussed and settled,
or unless I feel that it is good:
that I grew up caring for her instinct,
meaning ‘ታዝንብኛለች‘.
She believes in, I didn’t,
that I am the world.
While I am not even close
to be a piece of land
that she deserves to see.
If I smile, she would smile
if I frown, she still would smile
and try to infect me.
If she cries, the sky would,
or the sheet hold, on the bed
but I never saw.
/Yohanes Molla/
Long live my mom ❤ Happy mother’s day to all mothers!


May 3, 2017
ጠዪ በከፋ ቁጥር…
ማን ቃላት ቆጥሮ፣ ታሪክ ሰድሮ በአደራ አስረክቦታል? ማን ዜማ ሰፍሮ ሰጥቶታል? የት ከሰጠነው የሀሳብ ውሃ ልክ ነው ፈቀቅ አድርጎ መሰረት የጣለው? የትኛው የማዕዘን ድንጋይ ተናጋብን? በራሱ ፈቃድ፣ በራሱ ድምጽ፣ በራሱ ጊዜ፣ በራሱ ስም፣ በራሱ ገንዘብ ያሳተመው ሆኖ ሳለ፥ “ልጋታችሁ” ያለ ሳይኖር፣ ለምንድን ነው ለኪነ ጥበብ ወይም ለራሳቸው ጆሮ ተቆርቋሪ በመሆን ሳይሆን፣ በመንገብገብ ስሜት ውስጥ ሆነው ጥላቻን የሚያቁላሉ እና ክፋት የሚፈተፍቱ ሰዎች ከመካከላችን ሊፈጠሩ የቻሉት?
“ከዚህ በላይ ማድረግ ይችል ነበር። እንዲህ ቢሆን፣ እንዲያ ቢሆን… እዚህ ጋር ልክ አይደለም፣ በተሳሳተ መልኩ ነው የተገለጸው።” እያሉ በቀናውና ሰሪውንም፣ የሰሚንም ጆሮ በሚያንጽ መንገድ አስተያየት መስጠት፥ ሰሪውን ያሳድጋል፣ ለአድማጮችም የተሻሉና ዘመን ተሻጋሪ ሥራዎች እንዲሰሩ ያበረታልና መልካም ነው። በተለይ ከባለሞያ ሰዎች ይህንን እንጠብቃለን። (የጭፍን አድናቂ ስድብ ዶፍ ከባድ ቢሆንም በትንሽ ትንሹ መጋፈጥ ቢቻል እመኛለሁ። ባለፈው Abraham T. Woldemichael ቪኦኤ ላይ የሰጠውን አስተያየት ተከትሎ ዘለፋና ሙገሳ ያዘነበው ሰው አብዛኛው ቃለ ምልልሱን ያልሰማ እንደነበረ ስታቲስቲክሱን አይተናል።) ገንቢ የትችት ባህል ቢዳብርልን፣ ለሰራውም ሰው እውቅና መስጠት፣ ለሚመጣውም ትምህርት ይሆናል።
በሌላ ጎኑ፥ ከእነሱ የተለየ አስተያየት የሚሰጥን ሰው በስድብ እና በዛቻ የሚሞልጩ ሰዎችንም አወግዛለሁ። የምንወደውን ሰው በስድብ ካልሆነ ማስከበር የማንችል የሚመስለን ለምንድን ነው? ነፍሱስ ሰላም አታጣም? ማንስ ሰው ቢሆን፥ በርሱ የመጣ ሰዎች ሲሰደቡ እና፣ “አንተን ላወድስህ ኧከሌን ሰደብኩልህ” ተብሎ ይሸማቀቃል እንጂ ይደሰታል? ለምን የምናደንቀውን ሰው ለማሸማቀቅ እንደክማለን? ምን ይጎልብናል ሰው ያመነበትን ነገር እና የመሰለውን አስተያየት ቢጽፍ/ቢናገር? ደግሞ ምን አንገበገበን፥ የወደድነው ሰው ከዚህ በላይ የላቀ አቅም ላይ ቢደርስ?
ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ ለሁሉም ነገር ጊዜና ሁኔታ አለው። እሱን መጠበቅ ተሰሚነትን ከፍ ያደርጋል። ሲቻልና ሰሪው ፈቅዶ ሲያሳትፍ፥ ቀደም ብሎ አስተያየት መስጠት ነው። ካልሆነ ደግሞ ለቀጣይ ሥራ መማሪያ እንዲሆን ከስሜት ውዥንብር አርፎ መሬት እስኪያዝ ድረስ መጠበቅ ነው። ሙሽራን የሰርጓ ቀን አዳራሽ ውስጥ ሆና “ቬሎሽ ተንዘላዘለ፣ ሜካፕሽ በዛ” ብትባል ፎቶዋ እንዲበላሽ ከመጣር ያለፈ ሆኖ የሚፈይድ ነገር አለ?
በቃ የተመቻቹን መርጣችሁ ስሙ። ካልሆነም ላሽ በሉ። “አድናቂ ነን” ያላችሁም፥ ውዳሴ በመጻፍ ፋንታ፣ ሌላን ሰው በመስደብ የምትወዱትን ሰው ክብር ለማስጠበቅ አትሞክሩ። ትገመታላችሁ። ሁሉንም ሰው ካለምንም ተቆርቋሪ ስራው ያወጣዋል። ማንም ማንንም አያቆምም፣ አያራምድምም! ማንም በሰው ማጥላላት እንቅስቃሴውን አላቆመም። ማንም በወዳጆቹ ተሳዳቢነት ጸንቶ አልበረታም።
ጠዪ በከፋ ቁጥር ፍቅር በአምባው ላይ ይገናል! ልክ እንደዚሁ፥ ፍቅር አጨማልቆ እና ጨፋፍኖ፣ ልዩ የሆኑትን ማሳደብ ሲጀምር ተደናቂው ሰው ላይ ጭምር ጥላ ያጠላል። በፍቅር አምባገነንነት ውስጥ ግዞት ያለን ሰው ከስሜቱ እኩል እልህ ይዘውረዋል። ጥላቻም እንዲሁ ነው።
ስለዚህ እንተሳሰብ ጓዶች! ተቃቅረን ከምንኖር የተወሰኑ እርምጃዎችን ተቀራርበን የጋራ የሀሳብ ነጻነት ቤታችንን እንገንባ። ቢያንስ ፌስቡክ ያለውን ዘርፈ ብዙ ተጽህኖ እያየን ነውና፥ ፌስቡክ ላይ እንበርታ። ልክ እንደበፊቱ እንማማርበት።
ኢትዮጵያ ውስጥ ተቀብሮ ባለው እና ተከብሮ በዋለው ዓለማቀፍ የፕሬስ ነጻነት ቀን፥ ይህንን ስናገር ደስታ ይሰማኛል!

May 1, 2017
Aging…
Karma becomes more complicated with aging than it was ever. The World and it’s treasures – that were handful of our desires and joys in childhood, our ambitions to discover in prepubescence, and rebellion character in adolescent – gets to be infinite; and we want it all in vain that we stretch our hands to every direction, but we catch almost nothing. Our guts as a young to catch the fire gets down to inability to catch even the wind.
We know many people and many topics roughly, we socialize with many souls, but we feel that we have lost the grace; and yet, deep down, we want to selectively filter our circles… and we even are not close to what we want to know, and the kind of life we want to have. In fact, we know so much, but we ruin it all seeing what is not there. It is a different kind of complex and/or curse that we get pissed of against any kind of thing that reminds the fact that we are aging.
We try, we count our failures. We get prepared too much, we see our sweats. We want to laugh, we see the moments that we’ve wept. We want to shine, we stare at our wrinkles. We wish to keep our hair in style, but we see it balder and grayer. At times, we even laugh looking into the cosmetics we have bought. But when it comes to publicity, we change it all upside down and want to magnify the goods in us – that hasn’t been covered in the first place – at the cost of silencing youth. There will come fight within ourselves, and between emerging souls.
We, optionlessly and as a good virtue, become very specific to our activities, interests, and involvements, while we know many in general. And yet, at the eve of our adulthood and while on it, we find it hard to goodbye our youthhood. We rather live swinging between nostalgia and proving right that we are fine with the status quo.
We used to enjoy the moments… but as getting older, we preach much than we live; we speak more than we do; we talk more than we listen; we recall way less memories than we lived. We want to bury the young souls in the skin of our memories. We want to sing and let others about what was, than urging to fight for what is.
Regret couldn’t leave us alone; nor does ego. Time flies like were never before. Life becomes in a fashion of coffee and bear, and with bittersweet memories. Whatsoever, we die while explaining and proving ourselves right.
We can’t help it, with aging, life changes so fast, and memories fade away one by one. More powerful and wonderful minds are taking over our places. Time slip away things that we valued most, and our strength.
People become scared of being attacked personally; thus, they think they can skip from it by doing it on others. People start hating being judged, but they can’t stop hiding them selves in judgementalness. Fraternity and racism are most talked about topics, but few happen to be racist.
Good Lord!


April 26, 2017
አሰፋ ጫቦ ተገደለ ወይስ ሞተ?
በቬሮኒካ መላኩ [image error]
ባለፈው ወር አካባቢ የቦርከና ድረ ገፅ ባለቤት የእለት ስራውን እያከናወነ እያለ ከሌላኛው የአለም ጫፍ ከወደ አውስትራሊያ አንድ አጠር ያለች መልእክት ትደርሰዋለች ። ይች መልእክት ቦርከና የመልእክት ሳጥን ውስጥ በገባችበት ሰአት በሌላኛው የአለም ጫፍ አንድ በሙሉ ጤንነት ላይ የሚገኝ ሰው ዳላስ ውስጥ ምናልባት ራሱ ያፈላውን ቡና ከሲጃራው ጋር እያወራረደ ይሆናል ወይም ደሞ ብዙውን ጊዜውን የሚያዘወትርበት ቤተ መፅሃፍት ቤት ውስጥ ይሆናል ። ሁለቱንም ልማዶቹን በጣም ይወዳቸዋል ። ይህ ሰው በሙሉ ጤንነት ይገኝ የነበረው አሰፋ ጫቦ ነበር ።
መልእክቷ ምን ትላለች?
የቦርከናው ድረ ገፅ ባለቤት መልእክቷን ሲከፍታት እንደዚህ ትላለች
” ሰላም ጠና ይስጥልኝ ። ስሜ ግሪጎሪ ማኬንዚ ይባላል ። አቶ አሰፋ ጫቦ ጋር እንተዋወቃለን ። ሁለታችንም በዓለም በቃኝ እስር ቤት ጓደኛ ነበርን ። እባክህ የአቶ አሰፋ ጫቦን የኢሜይል አድራሻ ላክልኝ። ከምኖርበት አውስትራሊያ ወደ አሜሪካ ስለምጓዝ አሰፋን ማግኘት እፈልጋለሁኝ ። ሁለታችንም ስላረጀን የመጨረሻ እድሌ ሊሆን ይችላል ። ” ይላል
ይች አጭር መልእክት የደረሰችው የቦርከናው ድሜጥሮስ ብርቁ ወድያውኑ ለአቶ አሰፋ በፌስ ቡክ ሜሴጂ በኩል የሚከተለውን መልእክት ይልካል :
” ጋሼ አሰፋ ሰላም ነዎት ወይ? አንድ ግሪጎሪ ማኬንዚ የሚባል ሰው ከወደ አውስትሪሊያ ኢሜሎትን ጠየቀኝ ። ሰውየው በአለም በቃኝ እስር ቤት አብረን አሳልፈናል እያለ ነው ። ጓደኛየ ነበሩ ብሏል ። ግለሰቡን ያውቁታል ወይ ? ” በማለት ይፅፍላቸዋል ።
አሰፋ ጫቦም ስሙን በማስታወስ ” አዎን ! በማእከላዊ እስር ቤት ካገኘኋቸው አዋቂ የምላቸው ሰዎች አንዱ ነው ፤ ኢሜይሌን ስጠው ” ብለው መለሱ።
የአቶ አሰፋን መልስ ያገኘው የቦርከናው ድረ ገፅ ባለቤት አቶ አሰፋ የሰጡትን የኢሜይል አድራሻ ለግሪጎሪ ማኬንዚ ይልክለታል ።
ከቀናት በኋላም አቶ አሰፋ ወደ ቦርከና በላኩት መልእክት ” ግሪጎሪ ማኬንዚ በስልክ እንዳገኛቸው እና ወደ አሜሪካ ሲመጣ ዳላስ ቴክሳስ ለመገናኘት እንደተቀጣጠሩ ይነግሩትና ። ” ምስጋና ጨምረው ይፅፉለታል ።
ቀድሞ በተያዘው ቀጠሮ መሰረት አቶ አሰፋ ጫቦ እና “ሊጎበኛቸው” ዳላስ ድረስ የሄደው ግሪጎር ማኬንዚ ማርች 27 ቀን ዳላስ (ዳውን ታውን) ተገናኙ። በወቅቱ ሁለቱ ግለሰቦች ሲገናኙ አቶ አሰፋ ጫቦ ምንም አይነት የህመምም ሆነ የድካም ምልክት ያልነበራቸው እና እንዲያውም ለእድሜያቸው በጣም ጠንካራ የሚባል ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ነበሩ ።
ይሄንም የሚያረጋግጥ ምናልባት ከራት ሰዓት በፊት በሚመስል ሁኔታ አብረው የተነሱትንም ፎቶ ግራፍ አለ።
ሶስት ሰዓት በዘለቀው ቆይታቸው ፤ በእራት ሰዓት በአንድ የጣሊያን ሬስቶራንት ራት በልተው ፤ እንደገና ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘው ተለያዮ።
በማግስቱ አቶ አሰፋ ጨቦ ታመው ሆስፒታል ሄዱ። አቶ አሰፋ ጫቦ የመጨረሻዋን ኤሜይል ለግሪጎሪ ፃፉ “በምግብ መመረዝ” ። እንደታመሙ እና ስለህመማቸው ስሜት በዝርዝር ከፃፉለት በኋላ ዳግም ሊያገኙት ያልቻሉበትን ምክንያት ሆስፒታል መግባታቸው እንደሆነ ገለፁለት ። ”
ከአውስትሪሊያ ወደ አሜሪካ አቶ አሰፋን ጫቦን ለማግኘት ብዙ ሺህዎች ማይል አቋርጦ ዳላስ የደረሰውና አብሮአቸው ራት የበላው ግሪጎር ማኬንዚ ምንም የሆነው ነገር የለም።
ከዚያ በኋላ አቶ አሰፋ ከሆስፒታል አልተመለሱም። የግሪጎሪ ማኬንዚን እራት ተከትሎ ወደ ሆስፒታል የገቡት አቶ አሰፋ ከሆስፒታሉ ድነው ሳይሆን የወጡት ህይወታቸው አልፎ ነበር ።
እንቆቅልሹ የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው ።
ለአለፉት 40 አመታት አቶ አሰፋ ጫቦ ከተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልፅና ስውር ሽኩቻ ሲያደርግ ቆይቷል ። ዋጋም ከፍሎበታል ። ኢትዮጵያ ውስጥ እና በአካባቢው ያሉ የፖለቲካ ሃይሎች ወያኔ ፣ ኦነግ ፣ሸአቢያ ፣ ኢህአፓ እና መኢሶኖች አሰፋ ጫቦ ላይ ብዙ ክሶችን ፅፈውበታል ። እሱም የሚያውቀውን የድርጅቶችን ገበና ሳያቅማማ ሲፅፍ ነበር ። እነዚህ ፓርቲዎች በግለሰብ ደረጃ እንደ አሰፋ ጫቦ በእጅጉ የሚፈሩት አልነበረም፡፡ የሸአቢያን ፣ የወያኔንና የኦነግን ሴራ የሚያጋልጠው ፅሁፉ ፅፎ ካሰራጨና በመላው አለም መነጋገሪያ ከሆነ እንኳን ሁለት ወር አይሞላውም ነበር ።
አሰፋ ጫቦ በብሩህ አዕምሮውና በላቀ የእውቀት ደረጃው ብዙዎቹን ፖለቲከኞች በእጥፍ ድርቡ ያስከነዳቸው ነበር ፡፡ በዚህ የተነሳም አሰፋ ጫቦን ለአመታት ሲሰሩት የነበረውን ድብቅ ሴራ አውጥቶብናል ገና ወደፊትም ያወጣብናል እያሉ አጥብቀው ይፈሩትና አምርረው ይጠሉት ነበር ።
አሰፋ ጫቦ ጠንቃቃና የማስታወስ ችሎታ የነበረው አዛውንት ስለነበር በኢትዮጵያ ውስጥ እና በኢትዮጵያ ላይ የተሰሩ የድብቅ ሴራዎችን በጥንቃቄ ይዟቸው ኖሮ እያወጣ መጎልጎል ጀመረ ። በመለስ ዜናዊ የውሸት ክስ ሀገር የተባረረው አሰፋ ጫቦ በአሜሪካ አገር በስደት መኖር ጀመረ፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች ግን በብዙ ሺ ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሰው ሀገር የሚኖር ቢሆንም የአሰፋ ጫቦ ነገር እንቅልፍ ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ብዙ ጠቋሚ ምክንያቶች ነበሩ ።፡ አቶ አሰፋ ጫቦ በተለያዬ ጊዜ በሚፅፋቸውና በሚያጋልጣቸው ድብቅ ሴራዎች “የቀን ቅዠት ሆኖ እያባነነና እያስበረገጋቸው እንደነበር ይታወቃል። ሌሎቹንም የተደበቁ ሴራዎች እየፃፈ እንደነበር ተናግሯል ።
የአቶ አሰፋ ጫቦ የማስታወሻ ደብተር ብዙ ጉዳዮችን አጭቂ የያዘ እንደነበር መገመት አይከብድም ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ
እንደ ቆሰለ ጅብ የመበላላት አባዜ የተጠናወተው ነው ። ሸፍጡን እና ሴራውን ለመደበቅ አንዱን ገድሎ ስልጣኑን ማደላደል የተለመደ ነው ። ይሄ ለአመታት የተለመደ መርዘኛ ሂደቱን ቀጥሏል ። ከአንድ ሰሞን ከንፈር መምጠጥ ባለፈ “ ይሄ ሰው እንደት ሞተ? “ለምን ተገደለ?” በማን ተገደለ? ገዳዩ ለፍርድ ይቅረብ ወዘተ” የሚል ባህል የለንም ።
የአሰፋ ጫቦ ጉዳይ ገዳይ ተገዳይ ድራማ ያለበት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ በዚህ የገዳይ ተገዳይ ድራማ ውስጥ ብዙ ተሳታፊዎችን መጥቀስ ይቻላል ። አሰፋ ጫቦ በብእሩ ጫፍ ያቆሰላቸው ብዙ ናቸው ። “የትዝታ ፈለግ ” በሚለው መፅሃፉ CIA ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሱዳን ካርቱም ላይ መሰርቶት የነበረውን ጣቢያ አጋልጧል ።
“የተሰነይ ጉባኤ ” በሚለው ፅሁፉ ወያኔ ፣ሸአቢያ እና ኦነግ በኢትዮጵያ ላይ የሰሩትን ሴራ ለህዝቡ አሳውቋል ። ለወደፊቱም የሚያጋልጣቸው ብዙ ሚስጥሮች እንዳሉት እና እያዘጋጃቸው እንደነበር ነግሮናል ።
ስታሊን ከአባት ሀገር ያባረረውን ሊዮን ትሮትስኪ በብዙ ሺ ኪሎ ሜትሮች ርቆ በሰው ሀገር ሜክሲኮ የሚኖር ቢሆንም የሊዮን ትሮትስኪ ነገር እንቅልፍ ሊሰጠው ስላልቻለ በመጥረቢያ አስፈልጦ አስገደለው ። ወያኔ በኬኒያ እና በሱዳን የሚኖሩ ተራ ስደተኞች እረፍት ሲነሷት ወደ አገሮቹ ጎራ በማለት እንደምትገድል ይታወቃል ። CIA ም ቢሆን ጠላቴ ትንሽ ነው ብሎ አይንቅም ። ኦነግም አቶ አሰፋ ጫቦ በሚፅፋቸው መራራ ሃቆች ሲቆስል ኖሯል ። ዛሬ አሰፋ ጫቦን አጥተነዋል ነገር ግን ስለአሟሟቱ እንድንጠይቅ የሚያስገድዱ ብዙ ጥርጣሬዎች አሉ ። አሰፋ ጫቦ ተገደለ ወይስ ” ሞተ? ” ። ይሄ እንቆቅልሽ ይፈታ ዘንድ ሁላችንም መጠየቅ እና ትክክለኛውን መልስ ማግኘት አለብን ።


April 2, 2017
“Donkey Meat Up for Export, Slaughterhouse Opens” – Fortune
የአህዮቹ ገላ
ቀረበ ተልኮ፣ በጀማው ሊበላ
ታጨ ለስል ቢላ።
* * *
ተርፏቸው ሳይሰጧት
“ማር አይጥማት” ሲሉ
በስሟ ቀን ግፊያ
“አለች አሉ አህያ”
ብለው ሲደልሏት
ሲያነሱ ሲጥሏት በተራ በተራ
በኑረት ግፍተራ፣ ለተረት ሲሾሟት
ለሽሙጥ ሲድሯት…
በክፋት ታጭቀው በምሬት ሲያጉላሉ
ኖረው ኖረው መጡ
ስጋዋን ሊቆርጡ፣
ጌታዋን ሊረግጡ።
* * *
አህያማ ሞልቷል “አልጋ ሲሉት አመድ”
አቀማመጥ ጠፍቶት፣ ሰርክ የሚወላገድ፤
ወግ ደርሶት ገራፊ ወፌ ወፌ ላላ
ከፈሱ ተጣልቶ ሰው ገድሎ ሚበላ
ከባዶ አፍ ነጥቆ ቀፈቱን ሚሞላ፤
“ሰው መሳይ በሸንጎ”
በየወንበሩ ላይ፣ በየቢሮው ባልጎ
“በወል ስም” ተጠሪ፣ ኗሪ ተሸሽጎ።
/ዮሐንስ ሞላ/
[image error]
Fortune: Ethiopia is to export donkey’s meat, following the start of operations at a slaughterhouse in Bishoftu (Debrezeit) town, 48Km east of Addis Abeba.


ትውስታ… (አብደላ ዕዝራ)
‘ካፍ ካፍ የሚለቅም’፥ የሰው ዶሮ መጣ።”
ብዬ የዛሬ ሶስት ዓመት የለጠፍኩት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን ሀያሲ እና ፀሐፊ ጋሽ አብደላ ዕዝራ አስፍሮት ከነነበረው አስተያየት ፌስቡክ አስታወሰኝ። አስተያየቱን ከስር አስፍሬዋለሁ። ትንሹን ነገራችንን በቁምነገር መዝግበው እንደትልቅ እየቆጠሩልን የሚያበረቱንና የሚገስጹን ይብዙልን!
* * *
“ቀለማቱን ብቆጣጥር፥ ቤቱን ባስዉብ ባሰማምር፥
ቅኔ ዘረፋ ብማስን፥ ወርቁን ከሰሙ ብጋግር”… ያልከዉ ትዝ አለኝ።
“የብርሃን ልክፍት” እንደ ርዕስና ሽፋን የሚመጥነዉ የለም። ደበበ ቀድሞህ “የብርሃን ፍቅር”፥ አለማየሁ ገላጋይ ለጥቆ “የብርሃን ፈለጐች” ቢሉም፥ እንደ ርዕስ የልክፍትን [የብርሃን ልክፍት] ምትሃት ++ ያዉ እንደመጥምቁ በምናብ ወንዝ ተነክሮ ይሆናል። ጀርባዉም ይነባባል። ጨለማዉን ገምሶ የሚያንሰራራ የብርሃን ልክፍትአይለቅም።
የገዛሁት ሁለተኛዉን ዕትም ነበር። Oland በድሎሃል… ዉስጡን ለቄስ አስመሰለዉ፤ ግጥሞቹን ማለቴ አይደለም። scan ወይም ቀሺም ፎቶ ኮፒ መሰለ፤ በስንኝና በለጣቂዉ መካከል የተረሳዉ/የረገበዉ ክፍተት ገፀ ዉበቱን አደበዘዘዉ። የተፃፈበት ሆሄ ቢነበብም ቀለሙ [ካንተ ልዋስና] ወየበ። ሊትማንን “ገንዘቤን መልስ” አልለዉ-ጥቂት ግጥሞችህ እንቁ ሆነዉ ማን በፍራንክ የለዉጣቸዋል?
የመሰጠህን አንድ መንቶ ምረጥ በለኝ [] ሶስት ገፅ የወረረዉን የግጥሙን ድባብ የሚያባንንም፥ የሚያስተክዝ ነዉ። ተስፈንጥሮ የወጣ መንቶ አለ።
““እንኳን አደረሰህ” ከተንኳኳ በሬ
ያን ጊዜ እነቃለሁ፥ እሱ ነዉ ሀገሬ”
የተወሰኑ ግጥሞች ደግሜ የማነባቸዉ አሉ፤ ጥቂት የተንዛዙ እንደ መስለምለም ይከጅላቸዋል። ከመሰጠኝ አንዱ አሁን የሚታወሰኝ አጭር ግጥምህ ናት- “ፍርሃት” የምትለዉ። ለምን? እንዴት? ሰለመፅሐፍህ በሌላ ወቅት ሂስ መስል የተሰማኝን እገልጥለሃለሁ።
አሁን “ወርቁን ከሰሙ” የጋገርክበትን ከላይ የለገስከንን ዕምቅ መንቶ ልነካካዉ። አሻሚ ነዉ። ብርሃኑ ገበየሁ እንደሚለዉ “አሻሚነት ከአንድ ፍቺ በላይ ትርጓሜ መያዝ፥ ከግጥሙ ዐዉደንባብ በመነሳት ቁርጥ ያለ ትርጓሜ ለመስጥት አለመቻል” ነዉና እንደ አንባቢዉ ይነባበራል። ሁል ገድፈህ ሁሉ ቢሆን ዜማዉን አይጣረስም፤ ቀለም ሳይቆጠር እንዲሁ ሲደመጥ ያስታዉቃል። አለበለዝያ የ-ሁል- አደናጋሪነት የስንኙን ጠብታዎች ሊያመከን ነዉ።የተደራሲዉንም ትኩረት ይሻማል።
ገና እንደ አነበብኩት አዞ ትዝ አለኝ – አዞ እንባነቱ አይደለም – ሰፊ አፉን ከፍቶ ከጥርሶቹ መካከል አእዋፍ ጥሬ ስጋዉን ሲያስለቅሙ፤ ለአዞ እፎይታ ለነሱ መሰንበት። ይህ አንድምታ ነዉ።
“ካፍ ካፍ የሚለቅም የሰዉ ዶሮ መጣ” ግን ጉዳቱ ያሳስባል። አንድ የጥሬ ትርጉም “ያልተነካ ፥ አዲስ” ከሆነ አድገዉ ለወገን ምርኩዝ የሚሆኑትን ካከሰማቸዉ፥ በዘራፊ ማን ይመካል? ካፍ [ካፌ ባይሆንም] ከቀኝ ቢነበብ ፍካ ፍካ ሰለሚሆን ጮርቃዉን ብቻ አይደለም የፈካዉንም ሊለቃቀመ እንጂ። ይህ በደሉን አባባሰዉ። ከቀኝ ወደ ግራ ባይነበብም ሰሙ ወደ ወርቅ ሲመራም ነዉና ይነበብ።
ከጀርባዉ ከተስተዋለ ግን ብርቅ አንድምታ አለዉ። ዶሮ ጥሬ ለቅማ እኮ ነዉ [የአዳም ረታ ገፀባህሪይ – መዝገቡ- በልቶ የተደነቀበትን] የዕንቁላል ፍርፍር የምናገኘዉ። ጥሬ ተለቅሞ የሚጥም ከመቋደሻ እስከ ፈረሰኛ ለፋሲካ ወደ ብርሃነ ትንሳኤዉ የምንሻገርበት። “የሰዉ ዶሮ” የላመዉን፥ ያልሰለጠነዉን እየለቃቀመ እንደ ዕንቁላል እንደ ጫጩት ሊቀፈቅፋቸዉ ከቻለማ እሰየዉ ነዉ።
የግጥምህ አሻሚነት እየቆየ መዘርዘር፥ መነስነስ ይጀምራል። ይልቅ አሁን የመስፍን አሸብር ምጥን ግጥም ታሰሰኝ፤ በሱ ተመሰጥና ይብቃን።
“ጫጩቶቿን ብላ
ጭራ ልታበላ
“ቋቅ! ቁቅ!” እያለች፥
ይዛቸዉ ራቀች
ሄደች ኰበለለች፤
ያረባኋት ዶሮ
እንደወጣች ቀረች።”
—— // ——
ሀያሲ እና ፀሐፊ አብደላ ዕዝራ ግንቦት 28 ቀን 2008 ዓ/ም ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለየን። ለኢትዮጵያ ስነጽሁፍ እድገት ትልቅ ሀብት ነበር።
ዮሐንስ ሞላ's Blog
- ዮሐንስ ሞላ's profile
- 3 followers
