ዮሐንስ ሞላ's Blog, page 13
October 6, 2016
ግድቡማ
ቦንድ ግዙ ሲሉን ለልማት ነው ብዬ፣
ለካስ ለምሽግ ነው፥ ለሚሸጎጡበት…
ሲያጥለቀልቃቸው ጎርፍ ሆኖ ዕንባዬ!
ይኸው ደግሞ ወደንም ኾነ ተገደን፣ ላባችንን ጠብ አድርገን እያስገነባን ባለው “የአባይ ግድብ” ማስፈራራት ጀምረዋል። እንደምናየው እያስፈራሩን ያሉትም በራሳችን ንብረት ነው። የሕዝብ ብሶት ጦር ኾኖ ሲንቀለቀልባቸው፣ አባይን ተጋሸን (ጋሻ ሁነን) እያሉት ነው።
አሁን ነው “ወንድምና ወጥ ማስፈራሪያ ነው።” ብለው ሚሸልሉት። ግን እንጀራው ሲሻግት ወጡ በስትራው አይመጠጥ! እንጀራው ሲደርቅ ወጥ ትሪ አያስፈራራ! ደግሞ ተገንብቶ ኃይል ሲያመነጭስ ለእኛ ይትረፍ አይትረፍስ በምን እናውቃለን? እኛን በጨለማ “የሽንብራው ጠርጥር”ን እያስዘፈኑ ለሌሎች አፍሪካ አገራት መብራት እየቸበቸቡትም አይደል?
እኛ ቁርበት ላይ ስንቆራፈድ በስንትና ስንት ሚሊዮን ብር ቪላ አንጣለውም አይደል? ለቀድሞው ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ሳይቀር በወር 450 ሺህ ብር ቤት ኪራይ እየከፈሉ፣ ሰውዬውን ገዳም ገብተው ንስሀ እንዳይቀበሉ (እሳቸውን እንጥቀም ብለው ይሁን አከራዩን፥ እነሱ ያውቃሉ።) የከለከሏቸው በሕዝብ ገንዘብ አይደል?
ከዘፍጥረት አንስቶ፣ ገነትን ያጠጣ የነበረ፣ ከኤደን የፈለቀው የጊዮን ወንዝ እንደው ከአምባገነኖች ጋር ሕብረት አይኖረውም። ጩኸታችንንም ይዞት ይሄዳል። የምናምነው ያየናል። እንኳን ባሮቹን ሊፈጅ የመጣ መሰሪ ስርዓት፥ ይኹን ሲባል የኢያሪኮ ቅጥርም ከመውደቅ አልዳነም። ፈርኦን ከነጭፍሮቹም አልተረፉም። መልከ ጼዴቃዊ ሹመት ለግፈኞች ቃል አልተገባም።
የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ሁሉም ሂሳቡን ያወራርድ ዘንድ ግድ ነው!


October 4, 2016
ኢሬቻ

“ዋቃ ገለቶሚ” ልልህ አሰፍስፌ
መጥቼ ነበረ፥ ሰንበትን ቆጥሬ፣
ለከርሞው ልማጸን፥ ውዳሴ ሰፍሬ
ግጥሜን ደርድሬ፣ እልልታ ቀምሬ
ሀሴትን ቋጥሬ፥ የከንፈሬን ፍሬ፤
እኔን የቆሉበት ጢስ ሰማይ ላይ ወጥቶ፥
አጨናብሶህ መሰል፥ እንዳታይ አጥርቶ፣
ዘንድሮስ አልሞላ ቀጠሮ ታጎለ፣
ሳንተያይ ቀረ
ስጋ ዳገት ሰራ፣ ካፈር ተከመረ፤
ዋቃዮ የታለህ?
ብጣራም አልመጣህ ጭራሽ አትሰማ
በደም ተነከረ ያቀፍኩት ቀጤማ፤
ጽልመት ተነባብሮ ድቅድቅ ባለ ቁጥር፥
“ጽጌ ሊጠባ ነው፣ ሊነጋ ነው” ብዬ መጓጓቴም ከሳ፤
በነጎድጓድ ብዛት ሰማይ ሲተራመስ፥
ረግቶ ማያውቀው ሀይቅ፥ ክፉኛ ሲታመስ፥
“ምህረት ሊዘንብ ነው፣ ጥሩ ልጠጣ ነው”
ብዬ መጠበቄም፥ ጫነብኝ አበሳ፤
ኤሳ ጂራ ዋቃ?
ጋረደኝ ጨለማ፣ ደድሮ ተነሳ
የልቤ ክረምቱ በጣ’ይ ተከመረ፥
ብሶት እንባ መስሎ ካይኔ ተከተረ፤
ደሙን ተራምጄ ደም አደናቀፈኝ
እንባውን አልፌ እንባ ጠላለፈኝ፣
ዋይታውን ብዘለው ዋይታ ተቀበለኝ፥
ብሄድ ወደ ግራ፥ ብታጠፍ ወደቀኝ
ለቅሶና መከራ፣ ታጅቦ ጠበቀኝ፣
እስረኛው ጉያዬም በእሳት ተቃጠለ፥
በግፈኛው ሚዛን ሰውነት ቀለለ፤
ንገረኝ ጌታ ሆይ…
ስንት ተስፋ ይንጠፍ?
ስንት ጀምበር ይለፍ?
ስንት አበባ ይርገፍ?
ስንት ሰው ይሰዋ፣
እንዴት ይሙላ ጽዋ?
አይጥ በጠገበ፥ ስንት ይገረፍ ዳዋ?
ስንት ዳስ ይደርደር፣
ስንት ገጽ ይቧጨር?
ስንት ደረት ይፍረስ?
ስንት አጥንት ይከስከስ?
ከገጠር ከተማ፣ ስንሞት፣ ስንደማ፥
እንድታየን አንተ፣ ስንጮኽ እንድትሰማ?!
/ዮሐንስ ሞላ/


October 3, 2016
መርጠውና ለይተው፣ በእውቀትና በጥናት ላይ ተመርኩዘው ያደረጉት ነገር አይደለም። ልክ አፈጣ...
ስላልገደሉን ነው እንጂ ሁላችንም ላይ ተኩሰዋል። ስላልታሰርንላቸው ነው እንጂ ሁላችንም ላይ ሰንሰለታቸውን እያንሿሹ ሸልለውብናል። ስላልጣሉን ነው እንጂ ሁላችንንም ገፍትረዋል። ቅሬታን መግለጽና ይሻላል ያሉትን ሀሳብ መናገር ነውር እስኪመስል ድረስ በፍርሀት እና በሽብር ጠፍንገውናል። መፈጠራችንን እስክንጠላ ድረስ እርቃናችንን ለማስቀረት ደክመዋል።
እኛም አለን እስካሁን ከለቅሶ ለቅሶ እየዘለልን። ጨረስናቸው ሲሉን እንደ ምድር አሸዋ በዝተን እንኖራለን ገና!
እኔ ብሆን ኖሮስ?? እናቴ ብትሆን ኖሮስ?? ልጄ ቢሆን ኖሮስ?? ወንድሜ ቢሆን ኖሮስ?? እህቴ ብትሆን ኖሮስ?? ፍቅረኛዬ ብትሆን ኖሮስ?? የልብ ወዳጄ ቢሆን ኖሮስ?
“ማነሽ ባለተራ”
ጥርስ ውስጥ የገባሽ?
አናውቅም! ማንም አያውቅም!
እነሱም መግደልና ኡከት መፍጠር ሞያቸው ስላደረጉት እንጂ፥ ነገም ተቃዋሚውን መግደላቸውን እንጂ ማንን መግደላቸውን አያውቁም። ከገደሉ በኋላ ደግሞ ቁጥር መሸቀብና መቀርቀቡን ያውቃሉ። መዋሸቱን ያውቃሉ። እንጂ አገዳደሉ እንደገበያው ነው። ቤቱ ክፍት እንደተገኘበት ነው የጅብ አገባቡ። ጎረቤቱ እንደናቀው ነው የአጥር አነቃነቁ።
ሁላችንም በጋራ መነጋገር ካልጀመርን፣ ማውራት እና መደማመጥን ካላበረታን፣ እርስበርስ ካልተጠባበቅን ይጨርሱናል። በአንድነት ካልቆምን ለቅሷችን አያባራም፣ ድንኳናችንም አይፈርስም።
እግዚአብሔር ከተጎዱት ጋር ይቁም! በቃችሁ ይበለን!


October 2, 2016
They have killed many, they have knocked on many houses. ...
They raped a nation brutally, they have impregnated it breaking strong eggs with their inhuman sperms. They have killed, they have given birth to many. They didn’t know that throwing a seed means promising for it get rooted deep, and many of its kinds to come in fresh forms; as well, cutting the trunk is giving new branches a time of vegetating to trunks.
Through the blurs of our tears, we see many are joining in protesting the brutality, speaking up for those who can’t, and standing in solidarity with the victims. Now, concern will not be confused with politics, nor political awareness and activism will not be taken as a very wrong of the doers. Though a different kind of pain is inflicted in our hearts, eventually, knowing we all are mortals, we all know that it is a blessing in disguise.
They never loved us. They never loved to see us walking peacefully, to see us smiling, loving each one another, or having any undistracted day. Our peace is their mourn. Our holidays have been their peak times of terrifying us; our concerns and assemblies, their most terror. They were hate itself while we were celebrating Epiphany, Eid, Irreecha…even on the very secular great Ethiopian runs, they have been pains.
Demonstrations against violence of Saudi Arabia and Isis were among their public moments to show their sheer hatred for us. They have been distracting us with their guns, shackles, year gases, and physical and emotional tortures. Whether they saw us taking initiative to better community service plans, or they see us partake voluntarily, they never failed to see us with scorn. They never failed to prove us right that they have been consistent killers.
What has happened today is beyond our capacity to hold the pain, beyond what one can imagine, something that leaves one in shock even to properly cry about. I’m just acting weird; I can’t sit, nor I can stand properly…I can’t walk, nor loiter firm. I imagine how all you are feeling; it can’t be different, as our sufferings have been the same. They can’t hide it that it is a smart phone era that thousands have reported it with evidence. They couldn’t think, as we all have records in our minds. It is not about politics, but about humanity. It is not protesting, but speaking up against the devil itself.
But how many days shall we wait for?, how many nights to see us not being tortured to death? Is it the plan God? The beginning or the end? Revel, please. Egzio!
My heartfelt condolences to the innocent victims.
Death to bloody killers!


September 6, 2016
መንግስት ቢኖር…
“የገደለው ባልሽ
የሞተው ወንድምሽ፣
ሐዘንሽ ቅጥ አጣ
ከቤትሽ አልወጣ” ሆኖ አላመች አላቸው እንጂ፥ ለራሳቸው ፍጆታ ሲሉ እንደከዚህ በፊቱ ሁሉ እኛ የጠራነውን ብሔራዊ ሐዘን ያዳምቁ ነበር።
አሁን እንደው የመለስ ሞት በምን ሚዛን ተሰፍሮ ነበር፣ “በመንግስት ጥበቃ ስር ናቸው።” ተብሎ ሲታሰብ፣ በጥይት እና በእሳት ተጠባብሰው ከሞቱ ወገኖች ልቆ በዋሽንት ስንደነቁር የነበረው? ሲሆንስ አዲስ ዓመትን ጠብቆ እስረኞችን መፍታት የሚጠበቅ ነበር።
እሺ እሱም ቅንጦት ሆኖ ይቅር። የቤተሰብን ልብ ሰቅሎ ማሰቃየት ምን ይባላል? ባገራችን ደንብ እንደው የሰው ክቡርነት በሞት ደምቆ ይገለጻል። እርም ሳይወጣ ምግብ አይበላም። የከፋ ቅያሜ ቢኖር እንኳን አስከሬን ቆመው ያሳልፏል።
የሟች ወገኖች እናቶች እንዴት ሆነው ይኾን? የእናት እና የልጅ ተፈጥሯዊ ትስስር ጥልቅ ስለሆነ፥ የሞቱት እስረኞች እናቶች ይኽኔ ቁርጡን ሆዳቸው ይነግራቸዋል። (እናቴ በሌለሁበት ጠንከር ያለ እንቅፋት ቢመታኝ ታውቃለች።)
ታዲያ ግን ምን ብለው “ልጄ ሞቷል” ብለው ለቅሶ ይቀመጡ? ስሜቱን የማያውቅ ሰው እንደአሟራች ቢቆጥራቸውስ ይፈረድበታል። ምን ብለውስ “ልጄ ደህና ነው” ብለው ይረጋጉ። ስሜቱን የማያውቅ ሰው እንደግብዝ ቢቆጥራቸውስ ይፈረድበታል? ልጆቻቸው ሞቱ/ኖሩ ቁርጡን ሳያውቁ እንዴት ያንቀላፋሉ? ወዳጅ ዘመድ ጓደኛስ እንዴት እህል ይወርድለታል?
ሕዝብ በመንግስት በዚህ ልክ ይጠላል? “የድሃ ድሃዎች” አሉ ቃል ሲያሳምሩ እና ወሬ ለመቀሸር ሲሯሯጡ።
የክፉ ክፉዎች!!
ሕዝብ
——-
የእምቧይ ድርድር ካብ፥ እሾህ የማያጣ፣
ንጉሥ ሲደብረው፣
¬ ጭቃ ሹም ሲከፋ፣ ባለሟል ሲቆጣ፣
እንኳን ወሬው ቀርቶ፥ ዝምታው ‘ሚያስቀጣ፤
ኩራቱ ‘ሚያስጨንቅ — እንደ እመቤት ኩርፊያ፣
መቻሉ ‘ሚያስገፋ፣ ‘ሚያስደምር ከትቢያ፤
ወንበር ‘ሚያነቃንቅ፥ — የሰላሙ ዜና፣
መንግሥት የሚያሸብር፥ — የነፍሱ ጽሞና፤
ሳቁ ‘ሚያጠራጥር፤ ትንፋሹ ‘ሚያስገምት፣
እርምጃው ‘ሚለካ፤ ሩጫው ‘ሚያስፎትት፤
ሕዝብነት—
— ከንቱነት!
/ዮሐንስ ሞላ (2005) የብርሃን ልክፍት/


የንፍገት ጥግ
ገና በማለዳው፥ እንኳን የጻፈውን፣ ሊጽፍ ያሰበውን በፀረ ሽብር ህግ በቁም አሸበሩ… ‘በሽብርተኝነት ጠረጠርኩኝ’ ብለው ማለፊያውን ለቅመው፣ ሰብስበው አሰሩ፣…. ለተጠርጣሪው ሰው ማስረጃ ፍለጋ፣ ማስረጃ ቅመራ ላይ ታች ተባረሩ… በሰማይ በምድሩ ቧጠጡ፣ ዳከሩ… ወለሉን ቆፈሩ፣ ግድግዳውን ጫሩ… አልበቃ ብሏቸው ጊዜ ለፈጠራ፣ ለክስ ቅሸራ፥ በቀጠሮ መዓት፣ ገነቡ ተራራ… በእግረ ሙቅ እጅ አስረው፣ ከሰሩት አቀበት እያመላለሱ፣ አሳዩ መከራ…
ሲኖሩ ሲኖሩ…
ከእለታት ባንዱ ቀን፥ ‘እሳት ተነሳ’ አሉ ከእስር ቤት ምግብ ቤት… ‘ሊያመልጡ ሲሉ ነው’ ብለው በመተኮስ፣ የቻሉትን ጣሉ… አማራጭ በማጣት፣ የቀረውም ሸሸ ወደ ላንቃሙ እሳት… ‘ይህን ያህል ሞተ’ ተብሎ ተወራ፣ ከተጠቂውና ካጥቂው መንግስት ጎራ፣ ተዛብቶ ቆጠራ… ‘ከሞቱ ተረፉ’ የተባሉትንም ጭነው አጋዟቸው እስር ቤት ቀየሩ… በቤተሰብ ለቅሶ፣ በወዳጆች ዋይታ ታፈነ አየሩ… ቆዘመ መንደሩ…
ሳይነገር መርዶ… አስከሬን ሳይሰጥ… ከጥቃቱ የዳነም እንደተጨነቀ ሰላሙን ለማውራት… ተቆጠሩ ቀናት… ‘ቄሱም ዝም፣ መጻፉም’….. እርም ሳይወጣ፣ ያለው ሳይታወቅ ልብ እንደሰቀሉ… ‘አገሩ ሰላም ነው… በእውቀት ተቃወሙን’ ብለው አላገጡ፣ የቀለም ቀንዶችን፥ የቻሉትን አስረው፣ የቻሉትን ገፍተው እንዳላቀለጡ።
#Ethiopia
ምንም እንኳን የማውቃቸው ታሳሪዎች ባይኔ እየዞሩ እረፍት ቢነሱኝም፥ በሀቅ ሲመዘን ተጎጂው ሁሉ እኩል ነው። እግዚአብሔር ለተጨነቁትና ላዘኑት ሁሉ ብርታት ይስጥ። መርዶአቸው ባይሰማም፥ የሞቱትም በሰላም ይረፉ! የሰማዕትነትን አክሊል ያቀዳጅልን!


September 5, 2016
መስከረም ሳይጠባ!
እግዜር አልቃሽ ቁጠር
አስለቃሹን መዝግብ፣
በግርማ መንግስትህ
እግዜር ዋይታ ዘግብ፣
መከራውን አስብ፤
እግዜር ለቅሶ ለካ
ያልቃሹን ዐይን ንካ፣
ዳብሰው በመዳፍህ
አፍርስ ንቀል ሳንካ፣
ተቆጣው በቃልህ
አስለቃሹን ስበር፣
ደህነኛውን ተካ፤
አደይ አበባ እንካ፥
ውሰድ ጽጌያቱን
ተወው ያንን ዋርካ፣
በደግ ቀን ላንተ
ከዛፉ ጥላ ሥር
ውዳሴ እንድንሰፍር
ቃል እንድንቆጣጥር፣
አበባ እንድንለቅም፣
ጨዋታ እንድንገጥም
‘እኔክሽ እኔካ’
ጎንጉነን እንግጫ፥
የምናርፍ ጊዜ፥
ከጌቶች እርግጫ፤
ሲከፋን ተደፍተን፣
እንድናለቅስበት
ተሰብስበን በእምነት
ተጣምረን በእውነት፣
ደርድረን ምስክር
ከሰማይ ከምድር፣
እሮሮ እንድንቀምር፥
ተውልን ሰማዩን
ንቀለው ፀሐዩን
አዲስ ትከልልን፤
ሳናርፍ ከመከራ፥
እንባ ጋብ ሳይል
አንዴም ሳያባራ፣
ስንዘም፥ በምሽቱ
ስንወድቅ በጠራራ፣
“ማራናታ” ስንል
ሰርክ ስንጣራ…
ጊዜ ተፈትልኮ፣
ክረምት አልፎ በጋ፥
ሺህ መአልት ጨልሞ፥
አንዴም ሌት ሳይነጋ፣
ጳጉሜን ሆነ እኮ
ዘንድሮም ቀደመህ፣
አዲስ ዓመት መጣ፤
ሰለቸን ሺህ ዘመን
በ“እህህ” ማቃሰት
ጎዳን እምቧይነት፣
መኖር እሾህ ታክኮ
መቀለብ በጎመን…
አሮጌው ድስት ይውጣ፣
እግዜር ብረድስት ላክ፥
ብርቱ አብሳይ አምጣ፣
‘ሕዝብህን አድነው
ርስትህንም ባርክ’
ሰቆቃውን ክላ፣
ቤቱን ዘይት ሙላ
እግዜር ቀማሽ ስደድ፣
አልጫው ይጣፍጥ፣
ይነስነስበት ጨው፥
በሰላም ይላቆጥ፣
ይመለስበት ሰው፣
እንቁጣጣሽ እንበል
ዕንቁው ለዓለሙ፣
ጣጣው ያማረበት
የሰው ልጅ ሰላሙ!
ጅብ ከደጅ ሲያደባ
የሰው ደም ተጠምቶ
ይቀበር ከጉድባ፤
እግዜር ገድብ እንባ
እግዜር ሀሴት አስባ፣
መስከረም ሳይጠባ!
/ዮሐንስ ሞላ/


September 3, 2016
ስለደም…
ሕይወት እንደዚህ ናት። አንዳንዱ ‘ይጠብቃል’ ሲባል፥ ደም ለማፍሰስ በአዋጅ ታጥቆ ይነሳል። ሌላው ደግሞ ደም ለሚያስፈልገው ደም ለመሰብሰብ ያስተባብራል።
በተለይ በዚህ ጊዜ ብዙ ደም ያስፈልገናል። በየሁኔታው የተጎዱ ብዙዎች ስላሉ፣ መስጠት የምንችለውን ጥቂቱን ለመስጠት እጃችንን በመዘርጋት ብዙ ሕይወቶችን ከሞት እንታደጋለን። ከሰው ልጆች ጋር አብሮነታችንን በተግባር እንገልጻለን። ነገ ደግሞ አቡጊዳ ሮታራክት ክለብ 35ኛው የደም ልገሳ ፕሮግራሜን አከናውናለሁ ብሏልና፥ የምትችሉ ሁሉ በመሄድ በመልካሙ ተግባር እንድታሰተፉ ይሁን። ነገ የማትችሉ፣ ወይም በሌላ ቦታ ያላችሁ ደግሞ፥ በያላችሁበት ወይም በቻላችሁበት ጊዜ ደም እንድትለግሱና ለሰው ልጆች ደስታ አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ይሁን።
የነገው መርሀ ግብር ቦታ: ስታዲየም ብሔራዊ የደም ባንክ
ሰዓት: 2:30 – 12:00
አስተባባሪዎቹን እናመሰግናለን!


የቂሊንጦ እስር ቤት እሳት
ደግሞ እነ Daniel Berhane “ግርግሮች እየተቀዛቀዙ በመሄዳቸው የተደናገጡት የግንቦት 7 የውስጥ አርበኞች የሀገሪቱን እስር ቤቶች በእሳት መለኮስ ስራዬ ብለው ተያይዘውታል።” በማለት ተናግረዋል። እንዲህ ያለው “ሳያጣሩ ወሬ እና ውንጀላ” እሳቱ የሴራ መሆኑን ያመለክታል። (ከልምድ እንደምናውቀው፥ ምናልባት ጩኸት ለመቀማት እና ነገሩን ሁሉ ‘የአሸባሪዎች ዓላማ’ ለማለት? ምን ጣጣ አለው ለነሱ… በየታክሲው እና በየሆቴሉ ቦምብ እየጠመዱ ‘ፀረ ሰላም ኃይሎች’ ሲሉ እናውቅም የለ?)
በግንቦት ሰባት ስም ያሰሯቸውን እስረኞች ለመወንጀል ነው ‘የግንቦት 7 የውስጥ አርበኞች’ የሚባለው? ደግሞ ግንቦት ሰባት፥ ይኽን ያህል አቅም ያላቸው፣ ‘እስከሚኒስትር ዲኤታ ድረስ ሰርገው የገቡ’ የውስጥ አርበኞች እንዳለው እየገለጹ ከሆነ የመጠላትን ወሰን አያሳይም? (እንግዲህ ገና ትናንት ነው 100 ፐርሰንት የተመረጡት) ‘አሸባሪ’ ብሎ ስም ማውጣት ብቻውን ሰውን አሸባሪ ያደርገዋል እንዴ? ይኼን ያህል ኢህአዴግ በሊዝ አልገዛን። የምን ነገር ሲተበትቡ መኖር ነው?!
ለማንኛውም እርሱው ከየቤቱ እና ከማኅበረሰቡ ጉያ ፈልቅቆ ላሰራቸው ንጹሐን፣ ለያውም ገና በክርክር ላይ ያሉ፣ መንግስት ሙሉ ሀላፊነቱን ይወስዳል!!
ቸሩን ወሬ ያሰማን!
ቃጠሎውን በተመለከተ የዋዜማ ሬድዮን ዘገባ ቀጥሎ ያንብቡ።
(ዋዜማ ሬዲዮ) የቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ አጭር ዘገባ
ዋዜማ ራዲዮ-ተቃዋሚ የፓለቲካ አመራሮችን እና ጋዜጠኞችን ጨምሮ ከሶስት ሺህ በላይ እስረኞችን የሚይዘው የአዲስ አበባ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት በእሳት ጋየ።
በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ስር የሚገኘው የቂሊንጦ ጊዜያዊ የእስረኞች ማቆያ ዛሬ ጠዋቱን በግቢው በተነሳ የእሳት አደጋ ቃጠሎ የደረሰበት ሲሆን ቁጥራቸው ያልታወቁ ታራሚዎች መጎዳታቸውን የዓይን እማኞች ገልፀዋል፡፡
የእሳት አደጋው የተነሳው ጠዋት ሶስት ሰዓት ገደማ እንደነበር እና ቃጠሎውን ተከትሎም የተኩስ ድምፅ በተከታታይ መሰማት መቀጠሉን በአካባቢው የነበሩ እማኞች ለዋዜማ ተናግረዋል፡፡ እሳቱ የተቀሰቀሰው የቂሊንጦ እስር ቤትን ከሚጎራበተው የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ አቅጣጫ እንደሆነም ያስረዳሉ፡፡ ጥቂት ቆይቶ የአስተዳደር ቢሮዎች እና አዳራሽ ወደሚገኙበት ቦታ እንደተዛመተም ያብራራሉ፡፡
ለዩኒቨርስቲው የሚቀርበው የእስረኞች ቦታ በእስር ቤቱ አጠራር ዞን አንድ ተብሎ የሚታወቀው ቦታ ነው፡፡ በተለምዶ ወደ ሶስት ሺህ ገደማ እስረኞችን በውስጡ የሚይዘው የቂሊንጦ እስር ቤት በሶስት ትልልቅ ዞኖች የተከፋፈለ ነው፡፡ ምርጫ 2007ን ተከትሎ አነስተኛ የሆነ እና በቆርቆሮ የተሰሩ ማረፊያ ቤቶችን የያዘ አራተኛ ዞን የተገነባ ሲሆን በፖለቲካ ሰበብ ለእስር የተዳረጉ እሰረኞችን ከሌሎች ለመለየት በሚል አንድ አነስተኛ ዞን በቅርቡ ተጨምሯል፡፡
ቃጠሎው በየቦታው መስፋፋቱን ተከትሎ የእስር ቤቱ ፖሊሶች ዙሪያውን ከበው መተኮስ መጀመራቸውን እና የእስረኞች የጩኸት ድምጽ ከርቀት ሁሉ ጎልቶ ይሰማ እንደነበር በቦታው የነበረ የዋዜማ ምንጭ ይናገራል፡፡ ተኩሱ ለ40 ደቂቃ ያህል ግድም መቆየቱንም ይገልጻል፡፡ የተኩሱን ድምጽ የሰሙ በአቅራቢያው የሚገኙ የፌደራል የፖሊስ ኃይሎች ከጥቂት ጊዜ በኋላ መድረሳቸውንም ያስረዳል፡፡
በአንድ ኤፍ ኤስ አር ሙሉ የተጫኑ ፖሊሶች ወደ ግቢው ሲገቡ ተመልክቻለሁ የሚለው የዋዜማ ምንጭ በትንሹ በአምስት ፒክ አፕ መኪኖች የተጫኑ ተጨማሪ ፖሊሶችም ወደ ቦታው ሲያመሩ ማየቱን ይገልጻል፡፡
የተኩስ ድምጽ መሰማት ሲጀመር ከእስር ቤቱ አጠገብ በመሆን ለእስረኞች የሚፈቀዱ ሸቀጣ ሸቀጦችን የሚሸጡ የመንገድ ዳር ነጋዴዎች በፍጥነት መበታተናቸውን ሌላ የዓይን እማኝ ትናገራለች፡፡ የእስረኛ ጠያቂዎች ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ቦታው ሲጠጉ ፖሊሶች ይመልሷቸው እንደነበርም ታስረዳለች፡፡
እኩለቀን ሊሆን ግማሽ ስዓት እስኪቀረው ድረስ በእስር ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከፍተኛ ተኩስ ይሰማ የነበረ ሲሆን ወደ እስር ቤቱ የሚያስኬዱ መንገዶች ሁሉ በፀጥታ ሃይሎች ተዘግተዋል።
ቅሊንጦ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በርካታ የፓለቲካ አመራሮች ፣ የኢትዮጵያ የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ከፊል አባላት እንዲሁም ጋዜጠኞች ለአመታት የፍርድ ሂደታቸውን ታጉረው የሚከታተሉበት ስፍራ ነው።
በእስር ቤቱ ደንብ መሰረት የቅዳሜ እና እሁድ የእስረኞች መጠየቂያ ሰዓት ለግማሽ ቀን የተገደበ ነው፡፡ ጠያቂዎች ሁለት ሰዓት ተኩል አከባቢ ስማቸው እና የሚጠይቁትን ሰው አስመዝግበው ወደ ግቢው እንዲገቡ ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ቀናቱ የዕረፍት ቀን እንደመሆናቸው መጠን እና በርካታ ጠያቂዎች የሚስተናግዱበት በመሆኑ ብዙዎች በእስር ቤቱ አካባቢ የሚገኙት ማልደው ነው፡፡
በጠያቂዎች በኩል በዛሬው ዕለትም ተመሳሳይ ሁኔታ እንደነበር የዓይን እማኞች ይናገራሉ፡፡ በፖሊሶች አማካኝነት ከቦታው እንዲርቁ የተደረጉት ጠያቂዎች እና የአካባቢው ሰዎች በአንድ በኩል ከጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል እንዳያልፉ መደረጉን እና በሌላኛው አቅጣጫ ደግሞ ሄንከን ቢራ ፋብሪካ ጋር መንገድ መዘጋቱን ያብራራሉ፡፡
ከእስር ቤቱ የሚትጎለጎለውን ጭስ በርቀት ሆነው የሚያስተውሉት ጠያቂዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች አምቡላንሶች ወደ ቂሊንጦ እየተመላለሱ የተጉዱ ሰዎችን ጭነው በፍጥነት ወደ ህክምና መስጫ ቦታዎች ሲሄዱ መመልከታቸውን ያስረዳሉ፡፡ አምቡላንሶቹ መጀመሪያ ላይ በቂሊንጦ አቅራቢያ ወደሚገኘው ጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ሲገቡ ይታዩ የነበረ ሲሆን በስተኋላ ላይ ግን ሞልቷል በማባሉ ተጎጂዎችን ይዘው ወደ ቃሊቲ አቅጣጫ ሲሄዱ እንደነበር ይገልጻሉ፡፡
እስካሁን ድረስ ቁጥራቸው ያልታወቀ ታራሚዎች መጎዳታቸው ቢነገርም ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ግን አዳጋች ሆኗል፡፡ አደጋው መከሰቱን ያመነው የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል እና መቆጣጠር መስሪያ ቤትም ሶስት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞቹ ላይ ጉዳት መድረሱን ከመናገር ውጭ በእሰረኞች ላይ ስለደረሰው አደጋ ከመናገር ተቆጥቧል፡፡
በእስር ቤቶች ላይ የሚደርስ የእሳት ቃጠሎ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተደጋጋሚ ሲከሰት የሚስተዋል ጉዳይ ሆኗል፡፡ በዚህ ዓመት ብቻ በርካታ ሰዎች የተጎዱባቸው ተመሳሳይ አደጋዎች በጎንደር እና በደብረ ታቦር እስር ቤቶች ተከስቶ ነበር፡፡
የዋዜማ ሬድዮን የፌስቡክ ገጽ ይከተሉ።


September 2, 2016
NEW VOCABULARY TO YOUR DICTIONARY
1. an obsequious or overly deferential person; a toady.
2. unintelligible or meaningless speech or writing; nonsense; gibberish.
3. foolish or vacuous; puppet.
Example:
a) “HMDs are telling the oppressed majority of Ethiopia is at the good hands of the government that is known for its bloodiness”
b) “He was HMD enough to be a yes man whatsoever”.
c) “You are HMD to make any sense even to your girl friend.”
HMD (v.)
1. to serve somebody in a servile, degraded way; to act in a disgraceful toady way.
2. to speak unintelligibly, typically through fear or shock.
3. to held meeting at which people attempt to make contact with the dead.
Example:
a) “The prime minister HMDed to homicide innocents protesting against the barbaric government.”
b) The officers have been HMDing with the ghost of the late prime minister so as to continue his legacy of consistent and shameless tyranny.
HMD (adj.) 1. producing no result; useless.
2. ridiculously impractical or ill-advised.
3. not existing, or not actually present.
Example:
a) “An HMD attempt to calm down the protests with bullet.”
b) “He pretended to give an HMD solution.”
#Ethiopia


ዮሐንስ ሞላ's Blog
- ዮሐንስ ሞላ's profile
- 3 followers
