ዮሐንስ ሞላ's Blog, page 16

June 30, 2016

በአቅመቢስነት :-/

13507048_1604998063164033_3307705846976265661_nቀንቶት የሰው አገር ያየ ግን እንዴት ለአገሩ አይቀናም?? የሰውን አገር ስርዓት የተመለከተ ሰው እንዴት ለአገሩ ያንን አይመኝም?? የሰው አገርን የሰው ልጅ አከባበር ያስተዋለ ሰው ቀጥሎ እንዴት ሰውን ለማዋረድ (በዚያም ራሱን ለማዋረድ) ይፈቅዳል?? ባለስልጣናቱ በየስብሰባው፣ በየሽርሽሩ እና በየሰበብአስባቡ፣ በየተረተሩና ሸንተረሩ ሲንቀዋለሉ፥ እንዴት ነው… መንገዱን፣ ጽዳቱን፣ ስርዓቱን፣ ልምላሜውን፣ ጥጋቡን፣ ቅንነቱን፣ ሌላ ሌላ መልካሙን ሁሉ አገር ቤት ጭነው ስለመሄድ የማይቋምጡት??


 


ይገርማል! ሰው አገር ውስጥ ሰው ቢታመም፥ አስፈላጊውን ህክምና ከሰጡ በኋላ ነው ስለቢል የሚያወሩት፤ እንጂ ነፍስ ውጪ ግቢ የሚልን ሰው ህክምና አይነፍጉም። ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሰፈነባቸው አገራት፥ ፍትህ ይከበር ዘንድ፥ በወንጀል የሚፈለግ ሰው እንኳን እንደዋዛ በሞት ሲሰናበት ይበግናሉ። ቢችሉ አስታመው፣ አሻሽተው ነው ለፍትህ የሚያቀርቡት። (አሁን ለምሳሌ፥ ይሄን ሁሉ ነቀርሳ የተከሉት የቀድሞው ጠ/ሚ ሞት ልብ ተብሎ፣ በንጹህ አእምሮ ቢታሰብ እንዴት ያበግናል? እንዲሁ እንደጻድቅ ማሸለባቸው ሲታሰብ እንዴት ያንገበግባል? መቼስ ነፍስ የእግዚአብሔር ነውና ከሞት በኋላ አይፋረዱ ነገር!)


 


እነሱ ስለመንገድ እንጂ ስለተራማጅ ሰው ማውራት እርማቸው ነው። ስለህንጻ እንጂ ስለሰውነት መባዘን ሞታቸው ነው። …እንደው ህንጻና መንገዱንም በቅጡ በሰሩት እኮ! ሰው አገር ያለውን የመንገድ ስርዓት በቀዱት! ለፓርኪንግ (ለዚሁ ብቻ በታነጹ) ስንትና ስንት የተንጣለሉ ህንጻዎች ውስጥ ተሹሎክሉኮ መኪናውን ያቆመ ባለስልጣን፥ አገሩ ላይ ስለልማት ሲያወራ እንኳን፣ ጥራት እና ደረጃ እንኳን ህቅ አያደርገውም? “ልማት ልማት፣ እትት ብትት፣ ጸረ ልማት ኃይሎች…” ሲገርም! ሲያሳፍር!


 


“ኮንዶሚነም ተሰራ” ቢባል፥ ግማሹ በዝምድና እና በፖለቲካ ተሳትፎ ተደልድሎ የተረፈው፣ በስንትና ስንት ስለት እና ጾም ጸሎት በሚደርስ ዕጣ እንኳን፥ “ፈረሰ አልፈረሰ”፣ ሌት ተቀን በስጋት ነው። ደግሞ ሰው ስብሰባ ጠርቶ፣ ሰው አገር የታለፈ እና፣ ሌላ ሰው እንዲያነሳው በክብር የትም የሚጣል ጥሪት (ኩርሲ፣ ጠረጴዛ፣ መሶብ፣ ሶፋ፣ ብፌ፣ ቴሌቪዥን፣ አልጋ፣ መደርደሪያ፣ ሌላም ሌላም… ) ላይ ቤት መናድም አለ። የከርታታን ሰው፥ ተስፋንም፣ ጉጉትንም፣ ጥረትንም አብሮ መቅበር አለ። ከዚያ ሰላማዊን ሰው አውሬ ማድረግ! “ምን ልብላ” ብሎ ሥራ ሲፈልግ፥ ፈርዶበት አግኝቶት ለመንግስት ያፈነደደንና ሆዱን ለመጠቅጠቅ ሰፊውን ህዝብ በከንቱ ያስለቀሰ እና ያስቀመየን ምስኪን ፖሊስ ማስበላትና ደሙን በከንቱ ማፍሰስ![image error]


 


ከዚያ፥


 


“ሳሩን በልቶ ውሀውን ጠጥቶ የተኛውን በሬ፣


ጎትጉተው ጎትጉተው አደረጉት አውሬ” ይዘፈናል።


 


አንድን በሀሳብ የሚሞግት ተቃዋሚን ሰው፣ እሱንም በሀሰት ወንጅለው እንደማይገባው በግፍ ያንገላቱትን፣ ለህክምና እንዳይጓዝ በማገድ ማሰቃየት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ይሆናል?? ከአገር ቢወጣ ምን እንዳይጎዳቸው ነው?? መቼስ አገር ውስጥ ሆኖ ከእንግዲህ ድኖ ለእነርሱ ሰው አይሆናቸው። ወጥቶ እንዳይቀር ሰጉ?? ምነው ይሄን ያህል፥ ሺህ ዓመት አይኖር! ሺህ ዓመት በድለው እና አሳቅቀው አይነግሱ! በየትኛውም አገር ታሪክ ከዚህ ቀደም ሲበድሉ የነበሩት ቀናቸው ሲደርስ ከቅጣት አለፉ??


 


ወዳጄ ሀብታሙ አያሌው የምታምነው አምላክ ይቅደምልህና በምህረቱ ይጎብኝህ! ቅድስት ማርያም ትዳብስህ! ልባቸውን ያራራልህና ወጣትነትህ ለቤተሰብህና ለህልምህ ይትረፍ!

 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on June 30, 2016 20:10

June 26, 2016

የደንቢዶሎውን አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት አስመልክቶ በፌስቡክ የተሰጡ አስገራሚ ኮሜንቶች

ምትኩ ዳኜ እንዳጋራን 13516617_308246559519207_8521617860544782900_n


የበረራ አስተናጋጇ “ክቡራን የደምቢዶሎ ተሳፋሪዎች አዉሮፕላኑ በጭቃ ስለተቀረቀረ ወጥተን እንግፋዉ” ስትል አይታያችሁም?


በጭቃ ተይዞ ተሳፋሪው ወርዶ ግፋ ሁላ ሊባል ይችላል ማለት ነው…..ካልሆነ የትራክተር ጎማ ይግጠሙላቸው


Fake port


ጭቃ ማርሽ የሌለው አውሮፕላን ደምቢ ዶሎ መብረር የለበትም።


73 ሚልየን ብር ለደን ምንጠራ ነው? ሃሃሃ


በቃ ተገንብቷል አልኳችሁ ተገንብቷል፡፡ ሜዳው ራሱ ተገንብቻለሁ ብሎ እያመነ እናንተ ምነዉ?


አሞራ ራሱ እሺ ብሎ ሚያርፍ አይመስለኝም ክክክ


ዝናብ ሲዘንብ አውሮፕላኑ ቦቲ ጫማ አድርጎ እንደሚያርፍ ተስፋ እናደርጋለን


ቀልድ ነው አደል? በማርያም እኔ እልገባኝም ንገሩኝ


ማ ነበረ ከጥይትና ከርሀብ የተረፈውን ህዝብ በሳቅ እየገደሉት ነው ያለው?


EBC ደግሞ ገንዘቡን ወደ 33 ሚልዮን አውርዶታል። አብሽር ውለን ካደርን ገንዘቡ ወደ 73 ሺህ ብር መውረዱ አይቀርም። ዋናው ትዕግስት ነው!


ኪኪኪኪኪ….. ከመሀከላቸው አንድም ሰው የሚያገናዝብ ይጥፋ እንዴ? እረ እነዚህ ሰዎች ወደ ፃድቃኔ ማርያም ሄደው ሁለት ሰባት ከፍልጥ ጋር ሳያስፈልጋቸው አይቀርም፨


የእብድ ቀን አይመሽ አለች እማማ. . . ሳሩን ለማሳጨድ ነው 73 ሚሊዩን የተከፈለው?


hahahahah የእርሻ አውሮፕላን ነው?እያረሰ ነው እሚመስለው’ኮ


ዋውውው በቆሎ ቢዘራበት ምን ይመስላችኋል?


73ሚሊ.. አንድ አውሮፕላን ቢገዙበት አሪፍ ነበር ከጎደለ እንሞላላቸዋለን እንኩአን ይችን የስዊዝን ካዝና ሞልተነው የለ?


ኧረ ክረምት ነው ፕሌኑ እንዳይሰምጥና ሳይደላኝ እንዳልስቅ እባካችሁ


ኣውሮፕላኑ ችግር ገጥሞት የሆነ እርሻ ውስጥ ያረፈ ነው ሚመሰለው!


እረ ጎበዝ ይች አገር ወደ ሄት እየሄደች ነው???????? ያሳዝናል እንዴት የአንድ አገር መንግስት ሁሉ ደነዝ ሁሉ ድንጋይ ምነው ይሄ እኮ 21 ሴንቸሪ ነው ምነ እንደበግ ማሰቡን ብተውት!!!!!!


የተሰራው የፈረስ ጉግስ መጫዎቻ ነው። አይዞኝ እናት ሀገሬ


አውሮፕላን ጭቃ ላይም ያርፋል እንዴ!!!ወይ አለማወቅ፡፡


ምንድነው ነገሩ? ክረምት ክረምት የት ሊያርፍ ነው?


ከወያኔ ‘ብልጣ ብልጥ’ ስልቶች አንዱ እነሱ ፈትፍተው እየበሉ ሌላውን አፉን ወጥ መቀባት ነው። የአክሱምና የደምቢዶሎው የጢያራ ማረፍያዎች የዚህ ማሳያ ናቸው።


ለማስመረቅ እንኳን በኮብል ስቶን ሸፈን ቢያረጉት


ከአሁን በኃላ ወደኪስ ነው ወንድሜ እየተበደሩ swize ባንክ እንደ ባስኬት ቦል ፕሮጀክት እንዳትጠብቅ


የሌቦች ነገር ዛሚን ደግሞ ብትሰማ 112 ሚሊዮን ሳትል አትቀርም።


እነዚህ ሰዎች ሀገሪቷን በዕውቀት ሳይሆን በድግምት ነው የሚመሩት


ሰበር ዜና . በደምቢዶሎ። ከ33 ;42; 73 ሚሊዮን ብር በላይ የጨረሰው የጭቃ አየር ማረፊያ ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ ።


ግብርና መር—— አውሮፕላን ማረፊያችን


የሚሰማቸው ካገኙ ይህ አውሮፕላን ማረፊያ ከአፍሪካ 1ኛ ከአለም 2ኛ መሆኑ ይነገረናል ከአፍሪካ1ኛ ስል ምን ትዝ አለኝ ኢትዬዾያዊው ሰላይ ጀምስ ቦንድ ሞላ ግን እንዴት ነው ??!!!!!!


አስፓልቱ እኮ ከስር ነው እንዳይጎዳ ነው ከላይ ጭቃ የቀቡት እንዳይበላሽ!!! እርርርርርርርር….


እኔ እኮ በቴክኒክ ምክንያት የአንድ ገበሬ እርሻ መሬት ላይ ፓይለቶቹ ያሳረፍት መስሎኝ ነበር ።


የደምቢ ዶሎ ኤርፖርት ለትግራይ ህዝብ ምኑ ነው? ሟቹ ጠሚ በኮፒራይት እላይ ስሄድ እንዳይከሰኝ


ይሄን ሚሊዩን የሰው ስም አደረጉት እኯ ወይ ነዶ


አውሮፕላን በአፈር ላይ ማብረር ተጀመረ እንዴ እኛኮ ሁሌ አንደኛ ነኝ ታድለን


ታዲያ ለምንድነው ህዝብ ቢጠላቸው የሚደንቃቸው?


 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on June 26, 2016 08:00

June 25, 2016

ወይ ጉድ…

ከዓመት ከምናምን በፊት…


 


“አብሬያቸው ብሰራ” ከምላቸው፣ ጥሩ ስሜት ካሉኝ መሥሪያ ቤቶች መካከል በአንዱ የሥራ ማስታወቂያ መውጣቱን ጋዜጣ ላይ ተመልክቼ ለማመልከት አሰብኩና የትምህርት እና የሥራ ማስረጃዎቼን አደራጅቼ ሄድኩ። (መቼም አብዛኛው ቅጥር በፖለቲካ አቋም፣ በትውውቅና በዝምድና እንደሆነ ባላጣውም፥ በምናልባት ነበር ሙከራው።)


 


ከወጡት ሶስት የሥራ መደቦች እኔ ለማመልከት የፈለግኩት “managing director” ይል የነበረውን የሥራ መደብ ነበር። (ቀሪዎቹ ሁለቱ Data Encoder እና Secretary ነበሩ።) መስፈርቱን በበቂ ሁኔታ ስለማሟላ “ለቃለ መጠይቅ ፈተና ቢጠሩኝ እንኳን…” የሚል ጉጉት ነበረኝ።


 


ቢሮው ደረስኩኝና የሰው ሀብት አስተዳደሯን (መሰለችኝ) “ጤና ይስጥልኝ፣ የሥራ ማስታወቂያ አይቼ ለማመልከት ነበር።” አልኳት።


 


“Data encoder ነው?” አለችኝ። (ሶስተኛው መደብ ‘secretary’ ስለነበረ ሴቶችን ብቻ መጠበቋም አብሽቆኝ ነበር።)


 


“አይ ለማኔጂንግ ዳይሬክተር መደብ ነው።” አልኳት።


 


ገለማመጠችኝ አይገልጸውም።


 


“ማስታወቂያውን በደንብ አይተኸዋል? መስፈርቱ ብዙ ነው።” አለችኝ።


 


“አዎ! ስለማሟላ ነው የመጣሁት። ዶክመንቶቼን ይዣቸዋለሁ።” አልኳት።


 


“ማስተርስ ዲግሪ ነው የሚጠይቀው።” አለች።


 


“Sure, አለኝ” አልኩ።


 


“በአስተዳደር መደብ የሰራም ይላል…” አለች


 


“አዎ ሰርቻለሁ። እንደውም አሁን የምሰራውም በአስተዳደር መደብ ነው።”


 


አልተዋጠላትም። ዶክመንቶቼን እየተቀበለችኝ፣ “ብዙ ሰው አመልክቷል። ባትደክም ግን ጥሩ ነበር” ብላ አጉተመተመች። ማኅተሞቹን አፍጥጣ መመርመር ያዘች።


 


“ቆይ ግን ምን ዓይነት ሰው ጠብቀሽ ነበር?… ለማኔጂንግ ዳይሬክተርነት የሚያመለክተው ሰው እንዴት መሆን አለበት ብለሽ ነው?” አልኳት።


 


መልስም አልሰጠችኝም።


 


ተናድጄ ቀጠልኩ። “ሁኔታሽ ደስ አይልም። ብቀጠር እኮ ምናልባት አለቃሽ ነው የምሆነው።” አልኩ።


 


እርሷ እቴ ምንም አልመሰላት። (በልቧ “ኡኡቴ” ሳትልም አይቀር)


 


‘ስወጣ የቅርጫት ሲሳይ ታደርገዋለች።’ ብዬ ባስብም የተቀበለቻቸውን ዶክመንቶች ዝርዝር መመዝገቢያዋ ላይ መዘገበችኝ እና ፈረምኩ።


 


“ሳስበው ስራውን ብዙም አልፈልገውም። ለፈተና መጠራቴን ግን እፈልገዋለሁና ዶክመንቴ ቅጥር ኮሚቴው እጅ መድረስ አለመድረሱን እከታተላለሁ። ደህና ይዋሉ።” ብያት ሄድኩኝ።


 


* * *


 


ከወራት በፊት ደግሞ…


 


ለአንድ የአደራ መልእክት… የቤትና የቢሮ እቃዎች ሱቅ ሳይ፥ ተልኬ የነበረውን መግዛት የነበረብኝ እቃ ትዝ ብሎኝ ገባሁና ዞር ዞር ብዬ አይቼ፥


 


“ይሄ ስንት ነው?” አልኳት።


 


“ለቤት ነው የሚሆነው” አለችኝ።


 


በልቤ “ሆ” ብዬ… “አዎ እኔም ለቤት ነው የፈለግኩት።”


 


“ማለቴ ለመኖሪያ…”


 


“አዎ እኮ ለመኖሪያ። ቤት ያለውና የሌለው በድምጽ ይለያል እንዴ?” እንደጨዋታ ነበር ያሰብኩትና ያልኩት።


 


የተጋነነ ብር ነግራኝ… አያይዛ፥ “ግን ከዚህ ወረድ ብሎ አንድ ቤት አለ። ጠይቀሃል እዛ። ይረክስልሃል።” ብላኝ እርፍ።


 


* * *


 


በዚህ ሰሞን…


 


የሰው አገር ጠብ እርግፍ ሲታይ ደግሞ፥ የሚገዛውን እና የማይገዛውን፣ የሚመጥነውን እና የማይመጥነውን ሰው በዐይን አይተው የሚለዩት የአገሬ ልጆች በዐይኔ ዞሩ። የአገር እና የአገር ልጅ ነገር እንደው ባሰቡት ቁጥር ግርም ይላል፤ …ይኼ ይኼም እንደ ደህና ቁምነገር ይናፍቃል!


 


አልኩኝም… ወይ ጉድ!!!



 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on June 25, 2016 21:32

May 4, 2016

የብርሃን ሰበዞች

12321348_952128038241563_2108412543919940850_nእነሆ ሁለተኛ ልጃችንንም ወልደን ከእናንተ ጋር እንደባልቃት ዘንድ ጊዜው ቀረበ። “ምነው ከመጀመሪያው መጽሐፍህ በ3 ዓመታት ዘገየህ?” ላላችሁ ወዳጆች፥ ያው ያን በኦፕራሲዮን (C/S) ስለነበር የተገላገልነው፥ ጊዜውን አሳልፈን ብንባጠስም ለመቋጠር ትንሽ እምቢ ስላለን ነው። ሄሄሄ…


የምር ግን፥ ልክ እንደ “የብርሃን ልክፍት” ይኼም ከእርግዝናውና ከወሊዱ በላይ፥ ቀባብቶ እና አሽሞንሙኖ ከማኅበረሰብ ጋር የመደባለቁ ሥራ የበለጠ አድክሞኛል። ግን ሁሉም መለገምን ባለመሻት እና ወዳጆችን በማክበር ነው። እነሆ ሁሉም አልፎ፥ “በቅርብ ቀን” በማለት የሽፋን ምስሉን ቀብድ አስይዣለሁና እፎይታው ልዩ ነው። የበለጠው ደግሞ፥ ሰብሰብ ብለን በደመቀ ድግስ ስንመርቃት እንደሚኖረን ይሰማኛል።


የቀድሞው መጽሐፌ ላይ የተሰጡኝ አስተያየቶች እና አብሮነታችሁ ለዚህኛው ሥራ እንደረዳኝ አለመናገር ነውር ይሆናል። የብርሃን ልክፍት ካሰብኩት በላይ ተቀባይነት ማግኘቱ ለአዲስ ሥራ ያነቃቃኝ ቢሆንም፥ ይኼም ልክ እንደዚያኛው… “ከእኔ ይውጣልኝና ልገላገል”፣ “ወዳጆቼን ላስደስትና ጥያቄያቸውን በትህትና ልመልስ” “ተጨማሪ መጽሐፍ ቢኖረኝስ?”… ምናምን በሚል ተራ ስሜትና ሞቅታ ሳይሆን፣ ለስነጽሁፍ ዘርፍ ሊሰጠው የሚገባውን ክብርና ፍቅር በላቀ ለመረዳት በመጣር ነው። እናም “ይሁኑ” ያልኳቸውን ሰብስቤ፣ ከዘርፉ ባለሞያዎች እና ወዳጆች ጋር ተወያይቼ፣ “ይሆናል” ባልኩት አቀራረብ “የብርሃን ሰበዞች”ን አዘጋጅቻለሁ። በዚህም ላይ የሚኖሩትን አስተያየቶች ለቅሞ በመጠቀምና፣ በንባብና በልምድ በመታገዝ ደግሞ ወደፊት (እድሜና ጤና ከሰጠን) የተሻልኩ እንደምሆን አውቃለሁ።


ከህብረተሰብና ማህበረ-ባህላዊ ጉዳዮች ጋር ከማቀራረብ ባለፈ፥ ለብዙ የታፈኑ ድምጾች ልሳን በመሆን እያገለገለ ነውና ፌስቡክን ማወቅ ደስ ይላል። ብዙ ጊዜ ይፍጅ እንጂ፥ ፌስቡክን ቀርቦ አውቆ፥ ኗሪዎቹን ማስተዋልና እርስበርስ ተቀራርቦ በነፃ መማማር ደግሞ ይበልጥ ደስ ይላል። ያው ከነድክመትና ጉዳቱ ጋር! በጊዜ እየተሻሻሉና በአጠቃቀም ረገድ እየጎለመሱ ሲመጡ ደግሞ፥ ድካሙም ጉዳቱም አብሮ ይቀንሳል። (ይህን ያኔም ብዬው ነበር። ወደፊትም እለዋለሁ።) ታዲያ የ”3 ዓመታት” ያህል አድጌያለሁና፥ ድካምና ጉዳቱ ቀንሰውኛል ብዬ አስባለሁ። (ጊዜው ግን እንዴት ይሮጣል?)


ያኔ የእግዚአብሔር ሞገስ በፊቴ እንዲሆን ብቻ ተማጽኜ በጨበጣ የነበር የገባሁት። ይኸው ጸሎቴ ተሰምቶ ብዙ ሰው አተረፍኩኝ። ብዙ የመኖር ብልሀቶችን ለመድኹኝ። ያኔ ያልነበሩኝ ብዙ ነገሮችና ልምዶች አሁን አሉኝ። ዛሬ የሌሉኝ ደግሞ ነገ ይኖሩኛል። ሕይወቴ ላይ ብልጭ ብለው ድርግም ያሉትም፥ መቼም ባይረቡኝ ይሆናል። ዛሬም ዘወትርም የእግዚአብሔር ሞገስ በሁላችንም ፊት ይሁን። አሜን!


በጽሁፍና በመጽሐፍ ዝግጅት መንገዴ ላይ፣ በአንድም በሌላም መልኩ መልካም አስተዋፅኦ አድርጋችኋልና፣ በደግነትም በክፋትም፣ በንጹህ የወዳጅነት ስሜትም፥ በሽንገላም፣ በፌስቡክም በአካልም፥ ዙሪያዬ ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ከልብ ነው። እንኳን አወቅኋችሁ! …እንግዲህ “ይሁን” ስትሉ የ”በቀርብ ቀን“ ወሬውን በዙሪያችሁ ሁሉ አዳርሱት። ለወዳጆቻችሁ ንገሩ። የምረቃውን ቀንም ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ እና ስሜት እናሳልፈው ዘንድ፥ ጉጉት፣ በአሞራ፣ በጭልፊት እና በመሰል አእዋፍ አብረን እንጠብቃለን[image error]


ከበዛ ፍቅር እና ከበሬታ ጋር!


Push the news spread!


 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on May 04, 2016 14:43

April 11, 2016

“ትናንት” እና “ዛሬ”

ብዙ ጊዜ፥ የትናንቱን የማድነቅና የዛሬን ሰው የማኮሰስ ነገር አለ። በተለይ ከወዲያኛው ትውልድ ያሉ ሰዎች ያዘወትሩታል። ከወዲህም፥ “ዛሬ ቅቤ ንጠን ትናንትን እንቀባ” የሚሉ ንባብ ቀመስ ወጣቶች አሉ። እኔ የሰማኋቸው አባቶች ግን “ከትናንት ዛሬ ይሻላል” የሚሉ ይመስላል። ሁለት ገጠመኞቼን ላውጋችሁ። (ጨዋታዎቹ በጉራጊኛ ነበሩ። “ቃና ውስጤ ነው” ብለን ወደ አማርኛ መልሰናቸዋል።[image error] )


 


ከዚህ ቀደም፥ አንድ ለቅሶ ቤት ውስጥ “የዛሬ ወንዶች ለሚስቶቻቸውና ለልጆቻቸው” እንዲሁም “የድሮ ወንዶች ለሚስቶቻቸውና ለልጆቻቸው” የሚል ርዕስ ጉዳይ ላይ በእድሜ ገፋ ገፋ ያሉ አባቶች ይጫወታሉ። ሁሉም በሚባል ደረጃ፥ የዛሬውን አደነቁ። የእኛ ጊዜ ወንድ “ወተትሽ ገነፈለልሽ። ልጅሽ አለቀሰልሽ።” ነበር የምንለው። ጠግቦ ሰክሮ በረሀብ የዋለች ሚስቱን ልደብድብ የሚልም አለ።”


 


“ፍራንክ ይዘን ስለገባን እርሷን እንንቃለን። እንዳባካኝ ነው የምንቆጥራት። ሲታሰብ ግን፥ ውሎ የሚገባውን የወንዱን ስራ እርሷም ልትሸፍነው ትችላለች። ወንዱ ግን የእርሷን የቤት ስራ ሊሸፍን አይችልም። ዛሬ ባብዛኛው ያቅም ያቅሙን ሰርቶ ይገባል። ስንት አለሽ? እኔ ጋር ይሄ አለ ተባብለው ነው። ሚስቱ ብታረግዝ አብሯት የሚጨነቀው ብዙ ነው። ሀኪም ቤት አብሯት ይሄዳል። ለልጁ ሮጦ ይገባል። …አንዳንዱ ነገር ይበዛና ያሳቅቃል እንጂ የተሻሻለው ይበዛል።” ምናምን ሲሉ ነበር።


 


ዛሬ ጠዋት ደግሞ ዘመድ ሞቶ ለቅሶ ልደርስ ሄጄ፥ ተመሳሳይ ዓይነት የዛሬን እና የትናንትን የማወዳደር ውይይት ስቦኝ ጆሮዬን ጣልኩ። ይህኛው፥ “የዛሬ ወጣቶች ያላቸው የመተባበር እና ሰው የመርዳት ሁኔታ” እና “የድሮ ወጣቶች የነበራቸው የመተባበር እና ሰው የመርዳት ሁኔታ” የሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያጠነጠነ ነበር።


 


መጀመሪያ “ትናንት ይሻላል” “ዛሬ ይሻላል” የሚሉ ድምጾች ተደበላልቀው ነበር። ቆይቶ ምክንያት ሲደረደር “ዛሬ ይሻላል” ወደሚለው አዘነበሉ። “በእኛ ጊዜ ክፋት ኖሮም ሳይሆን ሰው እርዳታ የሚያስፈልገው አይመስልም። በዚያም ሰው ልርዳ ብለህ ብታስብ መረጃም አይኖርም። ቤትህ ከሞላ ሁሉም ቤት የሞላ ይመስልሃል። ቤትህ ከጎደለ ሁሉም ቤት የጎደለ ይመስልሃል። አሁን ሰው ዘግቶ ይኖራል ተብሎ ይታማል እንጂ፥ ያሁን ሰው የተሻለ ይግባባል። በኮምፑተርም በስልክም ይገናኛል። ችግርህን ካወቀ ድንጋይ ፈንቅሎ ይረዳሃል። ደግሞ ገመናህም ሳይዘራ በትንሽ ሰው ያልቃል። መንገድ ያጣል እንጂ ሩጫ አላነሰውም። ድሮ ልስራ ላለ አልጋ ባልጋ ነበር።”


 


እንዲህ ዓይነት አባቶች እና እናቶች ይብዙልን! ትናንትን እያጣቀሱ ከመውቀስ ባለፈ፥ ዛሬም ላይ ያለውን የተሻለ ነገር እየነቀሱ እውቅናን ቢሰጡ ለተሻሉ መልካምነቶች ያነቃቃል።


 


ከዛሬም ነገ ይሻላል!


 


እድሜና ጤና ይስጥልን!






 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on April 11, 2016 14:11

April 7, 2016

ድራማው የቀን ቅኝት ነው፤ “ማለቂያው ሩቅ ነው” ስልሽ፥ ወዳጄ!
ከ15 ሚሊየን ሕዝብ በላይ...

12936736_1353244648025346_6022529115159645969_nድራማው የቀን ቅኝት ነው፤ “ማለቂያው ሩቅ ነው” ስልሽ፥ ወዳጄ!


ከ15 ሚሊየን ሕዝብ በላይ በተራበበት አገር ውስጥ፥ ከአንድ ሺ ሚሊየነር ገበሬዎች ሸልመናል ይባልልኛል። ታዲያ ይኼ በአንድ ክልል ውስጥ ነው። የሌላውን የክልሉ ኮካዎች ሀላፊ ሰብስቦ ሲሸልመው ወሬውን እንሰማለን።


እንበል (let’s assume):


ያን ያህል ሚሊየነር ገበሬዎች አሉ። ሁሉም ያላቸው የሀብት መጠን አንድ ሚሊዮን በነፍስ ወከፍ ብቻ ነው እንበል። አንድ ሺህው በጋራ 1 ቢሊዮን ብር ሀብት ይኖራቸዋል ማለት ነው።


ታዲያ ይሄ ሁሉ ሚሊየነር ገበሬ ሞልቶ ረሀቡ እንዴት ተከሰተ?


“ድርቁ” አላልኩም። ድርቁ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው። ዝናብ ሲመጣ፣ ዝናብ ሲሄድ የሚሆን ነገር ነው። ረሀቡ ግን ክፉ ቀንን አስቦ ምግብ ያለማስቀመጥ ውጤት ነው።


በአንድ አካባቢ ይህን ያህል ሚሊየነር ገበሬዎች አሉ ማለት፥ እንደከተማ ለሙስና እና ለዝርፊያ የተመቻቸ ሁኔታ ስለማይኖር፣ ኑሮው ይቀራረባልና የተቀሩት በብዛት በሺዎች የሚቆጠር ሀብት ይኖራቸዋል።


የኑሮ መሻሻል እና የሀብት መብዛት ደግሞ የአስተሳሰብ አድማስንም ይወስናልና (and the other way round) እንዴት ይሄ ሁሉ ሰው “ለነገ” ብሎ የማስቀመጥ ስነልቡና ሳይኖረው ቀረ?


እሺ እሱም ይቅር፥ በቀዬው፣ በክልሉ ይህን ያህል ሰው ሲራብ፥ ገበሬው ራሱ ቢያዋጣ ችግሩን/ገመናውን እዚያው ለዚያው ይሸፍነው አልነበር?


እሺ ይኼም ይቅር፥ “ወጧ እንዳማረላት ሴት” የሀላፊዎቹ “እዩኝ፣ ስሙኝ” ምንድን ነው?


ለሽልማቱስ ስንት ወጣ?


 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on April 07, 2016 19:47

ከዚህ ወዲያ ሽብር?

“በኢንተርኔት አማካይነት የድምፅና የምሥል ጥሪዎችና መልዕክቶችን የሚያስተላልፉ አፕሊኬሽኖች፣ ኢትዮ ቴሌኮም ከውጭ ጥሪዎች ማግኘት የሚችለውን ከፍተኛ ገቢ እንዳስቀሩበት ተገልጿል።” ብሎ ተራ ንግግር ከየትም አይገኝም። አገልግሎት ሰጪ ከሚሰጠው አገልግሎት ጋር እንጂ፥ “እንዲህ ባይሆን ይሄን ያህል አገኝ ነበር” የሚል ‘opportunity cost’ ያሰላል እንዴ? ይሄ እኮ፥ “የዓለም የቴሌኮም አገልግሎት በእኛ ስር ቢሆን ኖሮኮ ከዓለም አንደኛ ሀብታሞች እንሆን ነበር።” እንደማለት ያለ ነውር ሀሳብ ነው።


 


“አሜሪካዊ ብንሆን ኖሮ እኮ ይህን ያህል ሰው አይራብም ነበር!!”


 


“በአሁኑ ወቅት ክፍያ ለማስከፈልም ሆነ በማጭበርበር ተግባር ላይ የተሰማሩትን ለመቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂ ባለቤት ነን፡፡ ነገር ግን ክፍያ ለመጣል አልወሰንም፤” ብሎ ንግግርም ሌላ የሚያሳፍር ነው። እንዴት ነው ነገሩ? ቴክኖሎጂውን መጠቀም/አለመጠቀማቸውን ሳያውቁ ነው እንዴ በሚሊዮኖች ከፍለው የቴክኖሎጂው ባለቤት የሆኑት? መንግስት ሳያውቀው ነው እንዴ ግዢ የሚፈጸመው?


 


“ከአፕሊኬሽኖቹ ባለቤቶች ጋር መደራደርና ከዓመታዊ የትርፍ ድርሻቸው ክፍያ እንዲፈጽሙ መግባባት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡ በተለይ በኢትዮጵያ ብቸኛው የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪ ኢትዮ ቴሌኮም በመሆኑ፣ ከአፕሊኬሽን ባለቤቶች ጋር የክፍያ ድርድር ማድረግ ለኢትዮ ቴሌኮም ጠቀሜታዊ ፋይዳው የተሻለ ከሆነ ቀላል አማራጭ እንደሚሆን አቶ አንዱዓለም ጠቁመዋል፡፡” ከዚህ ወዲያ ገዳይ ዜናስ መቼም አይገኝም። ሃሃሃ… ደግሞ ብቸኛ የቴሌኮም አገልግሎት ሰጪነት የሚያኮራ ሆኖ ነው?


 


ደግነቱ ነውራችን ሁሉ በአማርኛ ነው።


 


“ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የወጣበትን የቴሌኮም መሠረተ ልማት ያለባለቤቱ ዕውቅናና ተጠቃሚነት የሚገለገሉና ከፍተኛ ትርፍ ለራሳቸው የሚያካብቱ ናቸው፤”


 


ኧረ ሼ! ኢንቨስትመንቱ ከሕዝብ ኪስ አይደለም እንዴ?? እቁብ ገብተው፣ ቆጥበው የከፈቱት ካምፓኒ አስመሰሉት እኮ። ከፍተኛ ትርፉን የሚያገኘውና ለራሱ የሚያካብተውስ “የሚታለበው ላም” ቴሌ አይደለም?? የቴሌኮም አገልግሎቱ አልበቃ ብሏቸው ስልክ ወደ መቸርቸር የገቡት እነሱ አይደሉም እንዴ?? አዳዲስ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በመቀየር ሰበብ የapparatus ወጪ የሚያስወጡን (ለምሳሌ ከEVDO ወደ 3G ሲያሻግሩን) እነሱ አይደሉም?? ደግሞ በፈለጉት መንገድ ለሚቆርጡትና አሁን ተሞልቶ አሁን ለሚያልቅ ካርድ።



የዚህን ምስኪን ነዋሪ ኑሮን በግንኙነት ወጪዎች (communication cost) መደጎም ማሰብ ቢቀር፥ ከፍተኛውን ወጪ ለግንኙነት እያወጣን ባለበት ሁኔታ እንዲህ ያለ ነገር ግፍ አይሆንም? ደግሞ ግንኙነት ሲቀላጠፍ እና ሕዝብ የግንኙነት ወጪ ሲቀንስ ገንዘቡን ቀቅሎ አይበላው ነገር፤ …ስራ ይሰራል እንጂ?! ዓለማቀፍ የነዳጅ ዋጋ በጣም ወርዶ ባለበት ሁኔታ፥ “በፊት ስንደጉም የነበርነውን እያወራረድን ነው” በሚል ተልካሻ ምክንያት፥ በየወሩ ዋጋ እየቀያየሩ ሕዝቡን ማሸበርስ ምን ይባላል?


 


መንግስቱ ኃይለማርያምም መጥቶ “በፊት ስደጉም የኖርኩትን ሂሳብ አስልታችሁ ቁረጡልኝ” ይበላ!?


 


በmacro economics ጽንሰ ሀሳብስ ብናስበው ዓለማቀፍ የግንኙነት ወጪዎችን መቀነስ ማለት፥ ስራዎችን ከማቀላጠፍ ባሻገር፣ የዲያስፖራውን ወጪ በመቀነስ ሀገር ውስጥ የሚላከውን ገንዘብ (remittance) ማሳደግና የአገር ውስጥ እንቅስቃሴን መደገፍ ማለት አይደለምን? ታዲያ ይሄ “ከውጭ ከሚገኝ ገቢ ከ50 በመቶ በላዩ ዲያስፖራ የሚልከው ነው።” የተባለለትን የሀገር ሀብት ማሳደግ እንጂ ሌላ ምን ነገር አለው? ደግሞ ምን ያህሉ የስልክ ተጠቃሚ ኢንተርኔት ይጠቀማል?


 


“ኢኪዩፕመንት አይደንቲቲ ሬጂስተር” ደግሞ ሌላ ገዳይ ነገር ናት። አሁን እንደው የተሰረቁ ስልኮች ቴሌን አሳስበውት? ሴንሰርሺፕ እና ስግብግብነት ሲቀሸሩ እንጂ።


 


“አልጠግብ ባይ ሲተፋ ያድራል!”



 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on April 07, 2016 05:37

March 11, 2016

አንዳንዴ…

በሰላሙ ጊዜ የሆድ የሆዳችንን እንጫወት ነበር። ያኔ እኔና አንቺ አፍ አፋፍ፥ ሚስጥር የባቄላ ወፍጮ ነበረ። ሁለታችንም ጋር የሚያድር የለም፤ ጨጓራችን እስኪወቀር፣ ምላሳችን ከረጢቱ እስኪራገፍ ድረስ ተናዘን፥ በወሬ ዱቄት የታጨቀ ከረጢት ከረጢታችንን ሸክፈን እንሄድ ነበር።


ነገር ያጋጨን እለት ያቆርሽውን ሁሉ አውጥተሽ ትነቁሪኝ ጀመረ። (ማቆር መቻልሽ የልብ ልብ ሳይሰጥሽም አልቀረ።)


መጣላታችን ልብሽ ውስጥ ሲነደፍ አገር በምስጢሬ የወሬ ስንጥቁን፥ ኩታ ሸምኖ አለበሰ።


ወዳጅ ያፈራኹበትን ነጻነትና፣ ያኔ ያወራሁት ነጻ ወሬ ሰንኮፍ ሆነው ሰውነቴ ላይ ተሰኩ። ተራማጅነትንም እረፍትንም ነሱኝ። ወዳጁን እንደቀበረ ሰው ቁም ለቁም ጢሜን ነጭቼ አገጬን ተገጠብኩ።


ቆጨኝ።


ክፉኛ ቆጨኝ።


ማውራቴ ቆጨኝ።


መስማትሽ ቆጨኝ።


ማወቄ ቆጨኝ።


ምን ነበር ባላውቅሽ ኖሮ? አንቺን ከማውቅሽ ምን ነበር ሌሎች ሌሎች ሰዎችን ባውቅ?


ማመኔ ቆጨኝ።


መጣላት የለም ያስባለኝ አፍቃሪ ሞኝነቴ ቆጨኝ።


ጆሮ ስላለሽ ቆጨኝ።


አልዋሽሽም፥ አፍ ስላለኝም ቆጨኝ።


“የሽንገላ አንደበቶች ዲዳ ይሁኑ” ይላል መጽሐፍ። እኔ ደግሞ ቅልብልብ አንደበቶችም ዲዳ ይሁኑ አልኩኝ።


“ቆይ ለስንጣላ” ብለሽ የሰማሽኝ ይመስል ስንጣላ የሰማሽኝን ሁሉ ቃል በቃል ለማሳጣት ተጠቀምሽበት።


ሚስጥሬን አሸሞርሽበት። ገመናዬን ወዳጅ አፈራሽበት።


የቅርብ ነበርሽና አንቺ ብለሽ ማን ሊጠራጠር?


ባለጊዜ ገድ የሰመረለት አትራፊ ነው። ቢጨምርም ቢቀንስም ገዢ አያጣም።


የፈለግሽውን ጨመርሽ። የፈለግሽውን ቀነስሽ።


“አወራሽ። ለፈለፍሽ። ሞላ አገሩ ሰማ።


ግደይኝ አንቺ ልክ ከጠላሽኝማ” አልልሽም።


እሱ ዘፈን ነው። “እዬዬም ሲደላ ነው” ይባላል፥ እሱ ፍቅር ነው። እሱ የ”እፍታው” ውጤት ነው። የእፍታው ጊዜ እንኳንና ገድለሽ ሄደሽ “ግደይኝ”፣ ሌላ ሌላም ይባላል። “ተባብረን ካልገደልን”ም ይባላል።


“ቆዳዬ ተገፎ፣ ይሁንልሽ ጫማ፣

ስጋየም ይደገም፣ ላንቺ ከተስማማ”


ይሄን ያለው ዘፋኝ መቼም “ይቅር ይበለኝ” ብሎ ጣቱን ስንቴ ነክሷል? ፍቅር እፍታው ላይ ደስ ይላል። የጅንጀናው ሰሞን ዓለም ነው። እንደህጻን ባለ ንጽህና ቅድስናን ያስናግራል። “ይድፋሽ” እስኪመጣ ድረስ “ልደፋ፣ ልሙት” ያለ ነው። “ወይ አምላኬ” ብሎ ማማረር እስኪተካ ድረስ “I am lucky” ማለት ደንብ ነው።


የእፍታው ጊዜ፥ አመሉም፣ ቋንቋውም ጉራማይሌ ነው።


“ጉንፌን አውልቄ ለበስኩኝ ቦላሌ”


በፍቅር ስንነፋረቅ አንቺን እመስል ብዬ ልቤ ላይ ያደረግኩትን ጉንፍ አውልቄ፥ የልቤን ቦላሌ ጥለሽው ከሄድሽበት አንስቼ ለብሼዋለሁ። ውሰጅልኝ የልብሽን ጉንፍ!


ደግሞ ራቁቴን ስታስቀሪኝ የቦላሌና የጉንፍ ወግ ቀርቶ አገለድምበት የነገር ሽርጥ ፍለጋ ተፍጨረጨርኩኝ።


ቀን አስማምቶን ተዋውቀን ስንኖር የመሰለኝ፥ ውሸት መሆኑን ቀን አጋጭቶን ስንተዋወቅ ገባኝ።


በነገርሽ ላይ፥ ይህን ይህን ሁሉ ያወቅኹት ዛሬ አይደለም። ነገር ባጋጨን ቅጽበት ነው።


እናቱን ነገር!


ስጉ አደረገኝ። ቤቴ እንደተዘረፈ እንዲሰማኝ አደረገኝ። ራቁቴን አስቀረኝ። ሳይሞላ የሞላ ያስመሰለውን ጎኔን ሁሉ ገላልጦት አንዘፈዘፈኝ። ያለኝን ሁሉ ይዘሽብኝ ስትሄጂ ተሰምቶኝ “ሂጂ” ስልሽ አነባሁ። ሂጂ-አትሂጂብኝ መሳቂያ አደረገኝ።


ግን ውሸት ምን ይሰራል? “አትሂጅብኙ” እርቃኔን ለመጠበቅ ነበር። ሰው የሚስጥር ተካፋዩን ደፍሮ “ሂጂ” አይልም። ቢል ወየው ለራሱ! ሚስጥር መካፈሉ ቢቀርም ልማድ አለ። ልማድ አጉል ነው። “ለገና የገዛኸው በግ፥ ስጋ ስላለ ለጥምቀት ይሁን ብለህ ብትተወው፣ ለጥምቀት ለማረድ ያሳሳህና በግ አርቢ ሆነህ ትቀራለህ” ይላል ወንድሜ። የግጭት ማግስቱ ነጻነት የመስጠቱን ያህል፥ ከነገ ወዲያው ወፍራም ማቅ ያለብሳል።


ያኔ “ሰዶ ማሳደድ ካማረህ ዶሮህን በቆቅ ለውጥ” ነው ጨዋታው።


ይሄን ተረት የቀመረው ሰው፥ የእኔ ቢጤ ይመስለኛል። ሳይቸግረው ሰዶ ሚስጥሩን ጥበቃ ሲያሳድድ የኖረ የኔ ቢጤ።


ምን ታረጊዋለሽ?


እጣ ፈንታ ነው!


አንቺ ሳትኖሪ በፊት… ድሮ ድሮ ግን ሕይወት እንዴት ነበር? ውሎ ገባው የት የት ነበር? ላንቺ ሳልነግርሽ በፊት ሚስጥሬን የትኛው ቋቴ ውስጥ ነበር የምሸሽገው? ወይስ ካንቺ በፊት ሰማይና ምድሬ ላይ ሚስጥር አልነበረም?


ሚስጥር ማጋራትን ካንቺ መምጣት ጋር ተማርኩኝ።


ሚስጥር መጠበቅን ካንቺ መሄድ ጋር ቀሰምኩኝ።


ይብላኝ የሸራረፍኩትን ለምታገኘኝ ለባለተራዋ ውዴ! ይብላኝ በተንሸዋረረ ዐይን እያየሁ፥ በተሸራረፈ ልቤ ውሃ ለምጣጣ እኔ!


እርሳት እርሳት አሉኝ እንዴት እረሳለሁ፥

ሞኝነቴን ብንቅ፥ ወዴት እበልጣለሁ?!




 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on March 11, 2016 12:55

March 8, 2016

Celebrating wo/men…

Celebrate wo/men, celebrate yourself, live well…


 


We all should empower women that it means empowering ourselves; it is empowering the society; it it utilizing all our resources and excelling life; it is living life to the fullest; it is rationality; it is humanity; it is how it should gonna be. Come on!, how is life thinkable without wo/men? We should know this properly, we should tell the sky and the earth, and practice it duly.


 


Taking the lion share, no wonder, women should uplift themselves; they should uplift men; they should uplift the society; they should cooperate in the process of generation replacement, and nurture uplifted children as an already determined fate, with the God’s will; that they should say “NO” for any oppression by their most intimate men, by people that they plan and commit their life with; …nor they should oppress anyone, and be civilly and intellectually arrogant.


 


They shouldn’t expect a miracle to come their ways to triumph over life, nor wait for someone else to work for them; no one should expect of course! …we all should struggle rather; we all should get together, make comfortable ways and go through altogether. Then, the legacy for children will be a decent place, where life will be cherished, and death will be celebrated.


 


By the way, I’m not a feminist… I even am against its very inception (the way I understand it); though it is driven by an androist world, the concept irritates me at all. I’m a humanist rather. (…but, if being ‘feminist’ means, being an activist for gender equality, proudly, I’m one hell of it.) I can’t think segregating human fellows into women and men. Apparently, no one has contributed any for the gender s/he has, nor s/he has done fault to be born having the sex s/he has.


 


Wake up brother! “brother Jacob ;-) “, and uplift your home!, empower the executive of your home; never undermine her power, nor take her for granted; respect yourself and never objectify your woman, as saying ‘I love you’ for someone that yourself has dared to objectify is foolishness at its worst level. Never do that my man; never ever, even, when you think, on her foolishness.


 


Wake up sister! “sister ;-) “, and uplift your home and the lives inside it!, fortify your abilities, unleash the potentials in you, utilize resources, dig for opportunities to come your ways, be respectful, be responsible and trusted, …and meet your soul truly! …that you will give birth for &rear an uplifted, other things being equal!


 


To respect each one another, and to contribute for the construction of a better place to bring neonates to, ‘the sky is the limit’.


 


– I think!


 


Lots of love!


 


#makeithappen #internationalwomansday #IWD2016

 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on March 08, 2016 04:55

March 1, 2016

እንዳለመታደል…

12767525_991101850982528_2078982365_nአያቶቻችን፥ ደፍሮን የመጣን የጠላት ጦር ስለሰውነት ዋጋ ከፍለው በድል መልሰውት ዛሬም ድረስ አንገታችንን ቀና አድርገን የምንሄድበትን፣ በየትኛውም ቦታ “ኢትዮጵያዊ ነኝ” ስንል፥ ዝም ብሎ ሰው እንዳልሆንን የሚያስመሰክርልንን የድል ታሪክ አበረከቱልን።


ኢትዮጵያን ጠርተን ዓድዋን ያስታወስነው የውጭ አገር ዜጋ፥ በልቡ “ኖር” ብሎ ጎንበስ ቀና ይልልናል። – ይሄ ቁመቱ ነው።


ወገን፥ “ጨርቄን፣ ማቄን፣ ልጄን፣ ቤቴን” ሳይል፥ እስካፍንጫው ከታጠቀ ዘመናዊ ጦር ጋር በጦርና በጎራዴ ገጥሟል። አፍሮም አልገባም፤ በድል እንጂ! – ይሄ ጀግንነቱ ነው።


የአገር ሉአላዊነት እንጂ ብልጭልጭ ስልጣኔ አላጓጓውም። የሰው ልጆች ነጻነት እና ክብር እንጂ፥ ቁሳቁስ አላታለለውም። እኛ እንድንኖር እሱ አለፈ። እኛ እንድንቆም እሱ ወደቀ። – ይሄ ምስጢሩ ነው።


ይኸው እኛ ደግሞ “ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?” በማስባል ዝንታለም የሚያስደንቀውን የአድዋ ድል ታክከን በዘር ተከፋፍለን እርስ በርስ ስለጥላቻ እና ስለዘር፥ ዋጋ ከፍለን እንዋጋለን። ታሪክን ከባለታሪኩ መንጥቀን ለማላቀቅ ላይ ታች እንላለን። ሁኔታችን ሁሉ አዟዙሮ እንደማያይ ነው። ነገራችን ሁሉ ዋጋ እንዳልተከፈለበት ነው። ቆም ብለን የምናደርገውን ብናይ ኖሮም እንኳን በሌላ ሰው፥ በራሳችን ትዝብት ውስጥ መውደቃችንን እንገነዘብ ነበር። እውን፥ የአድዋ ድል የሌላ አገር ድል ቢሆን ኖሮና፣ ታሪኩ ተዘርዝሮልን ብንሰማው ኖሮ፥ አለመደነቅ እንችል ነበር?


አንዳንዴ፥ “ብዙ ያልተደረገልን ሰዎች ብንሆን ኖሮ፣ ብዙ ታሪክና ቅርስ ባይኖረን ኖሮ፣ ተፈጥሮ ለእኛ ባያዳላ ኖሮ፥ ምናልባት ዛሬን ወደ ስልጣኔ ለመሸጋገር እንበረታ ነበር ይሆን?” እላለሁ። ይህም የሞኝ ሀሳብ ነው፤ እንጂ፥ እንዲህ ያለ ድንቅ ታሪክ፥ ዓለም ሲሰማው ሲደነቅበት የኖረን ነገር ማን “የእኔ ባይሆን ኖሮ እበረታ ነበር” ይላል?


የጀግኖቹ በረከት ይደርብን!


#VictoryOfAdwa #Adwa120 #Ethiopia #የአድዋ_ድል


Graphics: Ashu




 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on March 01, 2016 13:51

ዮሐንስ ሞላ's Blog

ዮሐንስ ሞላ
ዮሐንስ ሞላ isn't a Goodreads Author (yet), but they do have a blog, so here are some recent posts imported from their feed.
Follow ዮሐንስ ሞላ's blog with rss.