ስለመውደቅ…

ሰፈሬ ልጅ ገና ሊወድቅ ሲያስብ፥


 


“አንተ ልጅ ዋ… ቀስ ብለህ ተጫወት…”


“ዋ ብያለሁ…”


“እሺ ኋላ እሪ ብትል ምናለች እንዳትል…”


“ትደፋና ኋላ…ዋ”


(“ውይ ተዪው አንቺ ደግሞ። ይጫወቱ እስኪ። ሸክላ ነው ልጅ ሁሉ ሲጫወት ተለይቶ ምን እንዳይሆን ነው? እሺ ከዚያስ…” የሚል ወሬ የተጠማ ድምጽ ፊቸሪን ሊገባም ይችላል።) ብዙ የማስጠንቀቂያ መዓት ይጎርፍበታል።


 


ልጁ ልጅ ከሆነና፥ አስጠንቃቂዋ እናቲቱ ከሆነች በዐይኗ እየተከታተለቸው ሲወላገድ ትወላገዳለች፣ ሲወድቅ ትወድቃለች። አይሞቀውም እንጂ፣ አያውቀውም እንጂ፣ አንቀልባ አልጣለችበትም እንጂ፣ እየሄደ መስሎታል እንጂ፥ በዐይኗ አቅፋው ነው የሚራመደው።


 


ከዚያ ተፍ ተፍ ብሎ ባፍጢሙ ይደፋላቸውና፥ አቀባብሎ እንደሚጠብቅ ሁሉ ሰፈሩ ባንድ እግሩ ይቆማል።


 


“ኡኡ…” ድብልቅልቁ ይወጣል።


የወደቀበትን አፈር መቃም ግዴታው ነው። አጉል አፈር አይንካኝ የሚል አፈሩን የተጠየፈ ካልገጠመው በቀር አፈሩን አቅምሶ ነው ብድግ ማለቱ የሚቀጥለው።


ከሩቅ ያዩና ያልደረሱበት “አፈሩን አቀመስሽው?” ይላሉ።


“እናትህ ትደፋ” (እንደእኔ ዓይነት ልጅ ሲሆን “የእርሶ እናት ትደፋ” ብሎ የሚሮጥበት አጋጣሚም ይኖራል።
 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on December 01, 2017 18:02
No comments have been added yet.


ዮሐንስ ሞላ's Blog

ዮሐንስ ሞላ
ዮሐንስ ሞላ isn't a Goodreads Author (yet), but they do have a blog, so here are some recent posts imported from their feed.
Follow ዮሐንስ ሞላ's blog with rss.