“እንደምን ነሽ ሸገር
የእነ ሮቤል ኪሮስ፣ የኮካዎች አገር”
ካለነገር አይደለም ሮቤልን (aka the whale) ጠቅሼ ነገሬን መጀመሬ። ስለስፖርት እና ስለዓለም አቀፍ ውድድሮች ውክልና ሲወራ፥ ያለውን የተበላሸ አሰራር መልክ በሱ ልክ ለዓለም ያሳየ የለምና ነው። ያው ኮካ ኮካ ነው። ድራሹ ይጥፋ!
ሰበቤ ደግሞ ፈረንሳይ ውስጥ በምትኖርበት አፓርትመንት ውስጥ በኤርትራዊ ወጣት በትራስ ታፍና፣ በተሸለመችው ዋንጫ ጭንቅላቷን ተመትታ የሞተችው የ27 ዓመቷ ኢትዮጵያዊት ዝናሽ ገዝሙ ናት። ሞቷ/አሟሟቷ እጅግ በጣም ያንገበግባል። 
Published on December 03, 2017 18:01