ስለደም…

ሕይወት እንደዚህ ናት። አንዳንዱ ‘ይጠብቃል’ ሲባል፥ ደም ለማፍሰስ በአዋጅ ታጥቆ ይነሳል። ሌላው ደግሞ ደም ለሚያስፈልገው ደም ለመሰብሰብ ያስተባብራል።


በተለይ በዚህ ጊዜ ብዙ ደም ያስፈልገናል። በየሁኔታው የተጎዱ ብዙዎች ስላሉ፣ መስጠት የምንችለውን ጥቂቱን ለመስጠት እጃችንን በመዘርጋት ብዙ ሕይወቶችን ከሞት እንታደጋለን። ከሰው ልጆች ጋር አብሮነታችንን በተግባር እንገልጻለን። ነገ ደግሞ አቡጊዳ ሮታራክት ክለብ 35ኛው የደም ልገሳ ፕሮግራሜን አከናውናለሁ ብሏልና፥ የምትችሉ ሁሉ በመሄድ በመልካሙ ተግባር እንድታሰተፉ ይሁን። ነገ የማትችሉ፣ ወይም በሌላ ቦታ ያላችሁ ደግሞ፥ በያላችሁበት ወይም በቻላችሁበት ጊዜ ደም እንድትለግሱና ለሰው ልጆች ደስታ አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ይሁን።


የነገው መርሀ ግብር ቦታ: ስታዲየም ብሔራዊ የደም ባንክ

ሰዓት: 2:30 – 12:00



አስተባባሪዎቹን እናመሰግናለን!


14192653_10208858338767262_8093716728756210687_n



 •  0 comments  •  flag
Share on Twitter
Published on September 03, 2016 08:26
No comments have been added yet.


ዮሐንስ ሞላ's Blog

ዮሐንስ ሞላ
ዮሐንስ ሞላ isn't a Goodreads Author (yet), but they do have a blog, so here are some recent posts imported from their feed.
Follow ዮሐንስ ሞላ's blog with rss.