“ሳይቃጠል…”

መቼም ከዛሬው “ሳይቃጠል በቅጠል” እና ከሰሞኑ የኢንተርኔትና ማኅበራዊ ድረገጾች አፈና የምንማረው፥ ማኅበራዊ ድረ ገጾች (በተለይም ፌስቡክ) እንደሚያጣጥሉት፣ ከቁብ የማይቆጥሩት ሳይሆን፣ በጣም የሚፈሩትና ሕዝብ በማንቃት እነሱ የፈጠሩትን የመረጃ እና የመማማር ክፍተት የሚሞላ መሆኑን… ያም በጣም የሚያስጨንቃቸው እንደሆነ… እኛም ብንሆን ስለብዙ ነገር ብዙ የምንልበትና፣ ብዙ ነገሮችን ለማየት የምናጮልቅበት መስኮታችን በመሆኑ፥ ከምንግዜውም በላይ፣ በሀላፊነት እና በጥንቃቄ በመጠቀም ጋንጩራቱን በቀላሉ ማንጨርጨር እንደምንችል ነው። በተለይ በዚህ የግል ፕሬስ ድርቀት ባለበት ወቅት የፌስቡክ አስተዋጽኦ ጉልህ መሆኑን ትኩረት ማድረግ እንደሚገባን ነው።
የለበጣ ተጠቅመን እንዲህ ያራድናቸውማ፣ ቅርጽ ቅርጽ ስንይዝ፣ ወሬያችንም ደርዝ ደርዝ ሲያበጅ፣ ቃላቶቻችን የተመረጡ ሲሆኑ፣ የውይይት ባህሉም ሲደረጅማ ጨርቃቸውን ጥለው ያብዳሉ። ዩኒቨርስቲ እያለን የተማሪ አመጾች ሲኖሩ ከማይረሱ የተማሪ ድምጾች መካከል ይህቺ ዝማሬ ነበረች። (ሀዋሳ የተማራችሁ ታውቋታላችሁ።)
ጥያቄያችን ኦሆ… ይመለሳል ኦሆ፣
ይመለሳል… ኦሆ!
ባይመለስ ኦሆ… ጉድ ይፈላል ኦሆ፣
ጉድ ይፈላል ኦሆ
እኛ ያለን ኦሆ… ወረቀት ነው ኦሆ፣
ኦሆ ወረቀት ነው!
የእናንተ ግን ኦሆ… መሳሪያ ነው ኦሆ
መሳሪያ ነው!
እንግዲህ ከቻሉ የንጹሐኑን ስጋ ትተው ሀሳቦችን ይቀጥቅጡ። ሀሳቦችን ይግደሉ። ጥያቄዎችን ያሰቃዩ። የንጹሕ ሰው ደም እንደው አንዱ ቢነካ ሺውን ይቀሰቅሳል! አንዱ ቢወድቅ እልፍ ሆኖ ያፈራል! ሰማየ ሰማያትን ሰንጥቆ ያስተጋባና አማልክቱን ያስቆጣል!
#EBC: Thank you for stressing on the fact that our cyber existence is stressful to the brutal government; and our proper usage matters towards the different kinds and levels of changes we seek. ሰሞኑን በተሰራው ማስታወቂያ መሰረት ብዙ አዳድዲስ የፌስቡክ አባላት እንደሚመጡ እናምናለን። (ልማት ቅብርጥሶ ለማለት የሚበተኑትንም ጭምር) I hate you tho. #IHateEtv!
#Bullies: come, try the ideas! Fight with the minds of the oppressed majority!
#Friends: ከአብዮተኛው ፌስቡክ ጋር ወደ ፊት (Y) (Y) Let’s socialize in a way that we can sustainably desocialize violence and oppression from our beloved country!
#Ethiopia #StopKillingCivilians


Published on August 13, 2016 21:23
No comments have been added yet.
ዮሐንስ ሞላ's Blog
- ዮሐንስ ሞላ's profile
- 3 followers
ዮሐንስ ሞላ isn't a Goodreads Author
(yet),
but they
do have a blog,
so here are some recent posts imported from
their feed.
