Martha H. Kidane46 reviews30 followersFollowFollowJune 5, 2022ከዚህ በፊት ካነበብኳቸው የአዳም ጽሑፎች ይኸኛው በመጠኑ ልዩነት የሚያሳይባቸው ነጥቦች አሉት። እስካሁንም ከውስጤ ላወጣው ያልቻልኩት እና በሚገርም ምስል ከሳችነት የተገለጸ የለውጥ ታሪክን ይዟል። ትረካው ማራኪ ነው።This entire review has been hidden because of spoilers.
Jared Donis331 reviews58 followersFollowFollowNovember 25, 2023አዳም ረታ “የቅልልቦሽ ግማሽ ጨዋታ” ብሎ በሰየመው የድርሰት ቅርጽ በታቦት ማደሪያ ሰፈር የሚኖሩ የአምስት ወጣቶችን ሕይወት የሚተርክበት ሌላው ድንቅ ስራው ነው። ይህ ድርሰት ጥልቅ የትራጀዲ ታሪክ እንደሆነ ያስተዋልኩት ሙሉውን መጽሐፍ አንብቤ ከጨርስኩ በኋላ ነው። ገና ላላነበቡት ሰዎች ስል ዝርዝሩን አልናገርም። በኢትዮጵያዊነታችን ይሁን በሌሎች ምክንያቶች በተገቢው ዕድሜ በሙላት መኖርን እና በሙላት ማፍቀርን ሳናይ ወይም ለመሞከር ፈርተን እንዲሁ ተነካክተን እንደምናልፍ፤ ገና በልጅነት ወደፊት ጸጸት እና ናፍቆት የሚጭሩብንን ገጠመኞች እንደምናስተናግድ እና አብዛኞቹ የአዋቂነት ዕድሜ ላይ የምንኖርባችው ልምዶቻችን ክሽፈት የወለዳቸው ፍልስፍናዎቻችን እንደሆኑ ተረድቼበታለሁ። እንዲያው ከመጽሐፉ ምንም የምወስደው አስተምህሮ የለም ብዬ ባስብ እንኳ ደራሲው ድንቅ አድርጎ ስለጻፈው በልብ-ወለድ ታሪክነቱ ብቻ የማነብበው ስራ ነው። የምንኖርበት ገሃድ ምን ያህል አስደናቂ ዝርዝር እንዳለው ቆም ብለን የምናጤነው እና እውነታው በሚገለጥበት የቋንቋ ጉልበት የምንደነግጠው በአዳም ረታ ስራዎች ውስጥ ብቻ ነው። አዳምም ታዋቂ ደራሲ ሆኛለሁ የሚል ትዕቢት ሳይዘልቀው በስሙ ብቻ ማሳተምና ገንዘብ መሰብሰብ ስላለበት የማይጽፍ ደራሲ መሆኑን በተደጋጋሚ አስመስክሮአል። በዚህ እጅግ አከብረዋለሁ። መክሊቱን ሁሌም እያሳደገ ከልቡ የሚጽፍ ሰው ነው። በዚህ ዘመን ኖሮ የእርሱን ስራዎች ማንበብ መቻልም መታደል ነው። እንደ ድርሰቶቹ ከሆነ በእግዚአብሔር ማመኑን እርግጠኛ ባልሆንም አዳም ሆይ እግዚአብሔር ባርኮህ እጅግ ብዙ ጽፈህ አስነብበን ብዬ መርቄዋለሁ።
ዘካሪ፤ስ1 reviewFollowFollowJuly 26, 2020how can i read this book without getting it?This entire review has been hidden because of spoilers.